Monday 27 December 2010

የሰይጣን መፈክር በዋሸንግተን ዲሲ ቅድስት ማርያም ቤተ መቅደስ (ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ)


የሰይጣን መፈክር በዋሸንግተን ዲሲ ቅድስት ማርያም ቤተ መቅደስ (ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ) -

Wednesday 1 December 2010

ጠልሰም በዲሲ ደብተራ


ጠልሰም በዲሲ ደብተራ -

Tuesday 30 November 2010

FAKE AMARAS LOST THE PLOT IN LONDON


FAKE AMARAS LOST THE PLOT IN LONDON -

Sunday 21 November 2010

LIDETU AYALEW FACES THE MUSIC IN LONDON


LIDETU AYALEW FACES THE MUSIC IN LONDON -

Sunday 14 November 2010

ቁጩ አማሮችና የ30ኛው ዓመት በዓላቸው


ቁጩ አማሮችና የ30ኛው ዓመት በዓላቸው -

Saturday 6 November 2010

ዳግመኛ ፈጣን ምላሽ የሚጠይቅ የኅብረት ጥሪ።

ዳግመኛ ፈጣን ምላሽ የሚጠይቅ የኅብረት ጥሪ።

የሀገራችንና የህዝባችን የፖለቲካና የኢኮኖሚ ሁናቴ ያገባናል በማለት ለሚከተታሉ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን የሀገሪቷ የፖለቲካ ምኅዋር ይህን ይመስላል ብሎ ገለጣ ለመስጠት መሞከሩ ለቀባሪው አረዱት እንዳይሆንብን እንሰጋለን። ስለዚህም የታወቀዉን ጉዳይ ደግሞ በመዘርዘር አንባቢን አናሰለችም።
ከዚህ ቀደም እንደገለጽነዉ ሁሉ ሀገራችን በአንድ ፈላጭ ቆራጭ ግለሰብና ድርጅት መዳፍ ዉስጥ ገብታ ትሰቃያለች። ያልተቋረጠ የሲቃና የመከራ ጥሪም ታቀርባለች። እኛን ልጆቻንም ትማጸናለች።

በተለይም ከ2010 ምርጫ በኋላ መንግሥት በወሰደው ባፈጠጠና ባገጠጠ አምባገነናዊ እርምጃ ሁሉንም ዓይነት ተቃዋሚዎች “ወግዱልኝ” በማለት በመንግሥት ተብዬዉም አፈራረጅ ህጋዊ ሆነ ህገ ወጥ በሰላም የሚታገል ሆነ በጠብመንጃ ሁሉን ተቃዋሚዎች አንድ ናችሁ ብሏል። አንድም የሚያጠራጥርም ሆነ የሚያፈናፍን ቀዳዳ እንዳይኖር በእብሪት ተወጥሮ ዘግቶታል። በሁሉም ተቃዋሚ ኃይሎች ላይ መሠሪ ሴራዎችን መሸረቡንና የባለጌ ዱላውንም መሠንዘሩን ቀጥሏል። ከእንግዲህ የቀረው የህብረትና የህብረት ትግል ብቻ ነዉ ብለን እናምናለን። ይህን የምንለው ያለበቂ ምክንያት አይደለም፤ ይህን የምንለው ይህ ጥያቄ ሕዝብ አጠንክሮ እየጠየቀው ያለ ጥያቄም በመሆኑ ነው። ለነገ የማይባል የሕዝባችን ጥያቄ ነው!! ታዲያ ይህን የሕዝብ ጥያቄ በበቂ ስንመልስ ነው ሕዝቡ ዳር እስከዳር አብሮን ሊሠለፍ የሚችለው። ስለገዥው አምባገነን ግለሰብና መንግሥቱ ምንነት፤ በሕዝቡ ላይ ስለሚፈጽሙት ግፍና በደል፤ ስለመብት እጦትና ጥሰት፤ ስለድንበር መሬታችን ለባዕዳን መሰጠት፤ ስለ ለም የእርሻ መሬት ለባዕዳን ስለመቸብቸቡ፤ ስለሀገራችን ሉዓላዊነት መደፈርና ክብርዋ መዋረድ፤ የዘር ጥላቻ በመራገቡ ስለሀገራችን ወደመፈራረስ አደጋ መገፋት፤ ስለከፋ ድህነት ዳር እስከዳር መስፋፋትና ስለናጠጡ ጥቂት ሃብታሞች ቅንጦት፤ ስለ ባዕዳን ጣልቃገቦች ጎጂ ሚና፤ … ወ.ዘ.ተረፈ እየተናገርን ይህንን ሁኔታ በኅብረት ትግል እናስወግድ ሲባል ልናመናታ አይገባም እንላለን።

ከዚህ ቀደም ባሰራጨነዉ “ፈጣን ምላሽ የሚጠይቅ የኅብረት ጥሪ” ላይ ሃሳባችንና እንዲሁም ይጠቅማሉ ያልናቸዉን ሀገራዊነትንና ዲሞክራሲያዊነትን እኩልነትን የሚያንጸባርቁ አራት ነጥቦች አቅርበናል። ከዚህ ቀጥሎ በመጀመሪያው ጥሪ ላይ የቀረቡትን ነጥቦች፥ መሰረታዊ እምነታችን ስለሆኑ፥ ማስገባት ተገቢ ይመስለናል።

፩. በኢትዮጵያ አንድነትና የግዛት ሉዓላዊነት ላይ ግልጽና የማያወላውል ጽኑ እምነት መያዝና ማሳደር
፪. በየድርጅቶች ውስጥና በምንሰባሰብበት የኅብረት ማዕቀፍ ዉስጥ ዴሞክራሲያዊ አሰራርን ለማስፈንና በአገራችንም የሕግ የበላይነት እንዲኖር ጸንቶ መታገል
፫. በኢትዮጵያ ሕዝብ መካከል ምንም ዓይነት አድላዊነት እንዳይኖርና ሁሉም በሕግ ፊት እኩል ዜጎች መሆናቸዉን ማመንና በተግባርም ማስረገጥ
፬. የህወሓት/ኢህአዴግ መንግሥትና ሥርዓት የአፈናና የጭቆና ሥርዓት በመሆኑ መለወጥና በዴሞክራሲያዊ አስተዳደር መተካት እንዳለበት ማመን

ለመጀመሪያ ጥሪያችን ከበርካታ ሀገር ወዳድና ከዴሞክራቲክ ግለሰቦች በጎ አበረታችና ጠቃሚ ምላሾች አግኝተናል። በጣም ገንቢ የሆኑ ምክሮችም ለግሰዉናል። ከሁሉም በላይ የተጀመረውን የኅብረት ምስረታ ጥረት ከግብ ለማድረስ በሚደረገው ታላቅ ተግባር ላይ ተባባሪነታቸዉን ገልጸዉልናል። ሁሉንም ከልብ እናመሰግናለን። በጀመሩት ቀና ጎዳናም እንዲቀጥሉና አብረን የምንችለውን ሁሉ እንድናደርግ እናሳስባለን። እስከዛሬ ድረስ ጥሪውን አግኝተውም ሆነ ስለ ጥሪው ሰምተው ለጥሪው አዎንታዊ መልስ ያልሰጡትን ወገኖች፤ በተለያየ መልክና ደረጃ የተሰባሰቡትንም ሆነ ገና ያልተሰባሰቡትን፤ ይህንን ሀገራዊ ተግባር እንዲቀላቀሉና የበኩላቸዉን እንዲያደርጉ በአክብሮት ወገናዊ ጥሪ እናቀርባለን።

ለጥሪያችን በጎ ምላሽ በመስጠት፥ በኅብረት ምሥረታው ተግባር የባለቤትነት ድርሻችሁን በመውሰድ አብሮ ለመጓዝ ለወሰናችሁ ድርጅቶች አክብሮታችንን እንገልጣለን። ለምትቀርቧቸዉና ለምትግቧቧቸዉ የመሰባሰቡን ዓላማ በማስረዳት ኢትዮጵያዊያን በአንድ ጥሩ ውጤት ሊያመጣ በሚችል የአንድነት ሃይሎች ጥላ ሥር ይበልጥ እንድንሰባሰብ ጥረታችንን እንቀጥል።

ዛሬም እንደ ትላንትናው ለሀገር ወዳዱና ዲሞክራሲያዊ ለሆነው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ጥሪያችንን እናድሳለን። አንዳንዶቻችን በነጠላና በየግላችን የምናደርገው ጉዞ ዉጤት ያመጣል ብለን ብናስብም እንኳ እስካሁን ያለው ተሞክሮ የሚያስተምረን ሃሳብንና ኃይልን በአንድነት አስተባብሮ ከመታገል የተሻለ አማራጭ እንደሌለ ነው። ሕዝቡም በሙሉ ልብ ሊሳተፍ የሚችለው ያኔ ነውና!!

ስለዚህም የጋራ እናታችን የሆነችው ኢትዮጵያ በጭንቅና በመከራ ሲቃ ተቀስፋ ተይዛለች። እኛም ልጆቿ ጥሪዋን በመቀበልና እምባዋንም በማበስ አቤት እንበላት።

አድራሻችን
 ኢ--ሜይል-- consult4eth@gmail.com
 ቴሌፎን ---
 ከአውሮፓ ሲደወል 0039/329-784-6515
 ---ከአሜሪካና ካናዳ 011/39/329-784-6515

Tuesday 2 November 2010

KESIS ASTERAYE ON NOVEMBER 2005 MASSACRE


IN REMEMBERANCE OF MARTYRS OF NOVEMBER 2005 -

Tuesday 19 October 2010

ሽምግልና


SHIMGLINA -

Thursday 14 October 2010

ገለልተኛ


GELELETEGNA -

Saturday 9 October 2010

“በዕንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ”

በዛብህ በላቸው።

አባቶች፣ በክፉ ነገር ላይ ክፉ ነገር ሲያዩ “የግፍ ግፍ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ይላሉ”። በወይዘሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ ላይ፣ ወያኔ ያወጣውን መግለጫ፣ እንደዚሁ ነው። እንደገና መዘርዘር የሚያስፈልግ ባይሆንም፣ በቆራጥ ታጋይነት ከትግል ባልደረቦቿ ጋር ስትታገል አደገኛ ተቃዋሚ ሁና በመገኘቷ፣ እዝብን በአደባባይ የጨፈጨፉት ወንጀለኞች በአገር ክህደት ሳይቀር ከሰዋት፣ በቃሊቲ ወህኒ ቤት ተሰቃይታ በምሕረት ሽፋን፣ ከሌሎች ጋር እንደወጣች ይታወቃል። የተለቀቀችበትንም ምክኒያት በሕዝብ ስብሰባ ተጠይቃ ስታብራራ፣ በምሕረት መወጣቷን አምና ግን ሽማግሌዎች ባቀረቡት ሰነድ ላይ መፈረሟን ብቻ አረጋገጠች። ይኽ እንደ ወንጀል ተቆጥሮ፣ በሕግ የተሰጣት ምሕረት በማንአለብኝነት ተሽሮ፣ ለሁለት ዓመታት ያህል፣ ተሰቃየች። ከአቅሟ በላይ ጨከኑባት፣ አደቀቁአት።
ተሰቃየች ሲባል በተለመደ አነጋገር አይደለም። ያየችው የቁም ስቃይ ነው። ከሕጻን ልጇ፣ ከደካማና ባልቴት ወላጅ እናቷ፣ ከቤተሰብ፣ ከወዳጅና በተለይም አምናበት በቆራጥነት ከምትመራው ድርጅቷ ነው የተለየችው። የታሰረችው እንደሰብዓዊ ፍጡር አይደለም። ብቻዋን በጠባብና ጨለማ ክፍል ያለጠያቂና አነጋጋሪ ነው። በእስር እንዴት እንደቆየች ከሷ በስተቀር ሊገልጸው የሚችል ፍጡር አይኖርም። ቢቢሲ ሲጠይቃት ግን፣ በአንድ አጠቃላይ ቃል፣ “horrible” – “አሰቃቂ” ነበር ብላለች። ሊገለጽ የማይቻል ማለት ነው።
ምናልባት፣ የነበረችበትን የእስር ቤት ሁኔታ፣ ታላቁ ታጋይ ኔልሰን ማንዴላ በዘረኛው መንግሥት በተመሳሳይ እስራት፣ ያሳለፉት ስቃይ በመጠኑ ሊገልጸው ይችል ይሆናል።
“For the next few weeks I was completely and utterly isolated. I did not see the face or hear the voice of another prisoner. I was locked up for 23 hours a day, with 30 minutes of exercise in the morning again in the afternoon. I had never been in isolation before, and every hour seemed like a year. There was no natural light in cell; a single bulb burned overhead 24 hours a day. I did not have a wrist watch and often thought it was the middle of the night when it was only late afternoon. I had nothing to read, nothing to write on or with, and no one to talk to. The mind begins to turn on itself, and one desperately wants something outside oneself on which to fix one’s attention. I have known men who took half a dozen lashes in preference to being locked up alone. After a time in solitary, I relished the company even of insects in my cell, and found myself on the verge of initiating conversations with a cockroach.” (Long Way to Freedom, Nelsen Mandela, pp 36-39, 1994)
“ለሚቀጥሉት ጥቂት ሳምንታት ሙሉ በሙሉ፣ በይፋ ብቸኛ ሁኜ ነበር። የሌላ ሰው ፊት አላየሁም፣ ድምጽም አልሰማሁም። በቀን ለ23 ሰዓታት ይዘጉብኝ ነበር። ከጠዋቱና ከሰዓት በኋላ የግማሽ ሰዓት እንቅሰቃሴ በስተቀር። ከዚያ በፊት ብቸኛ ሁኜ አላውቅም። በመሆኑም እያንዳንዱ ሰዓት እንደ ዓመት ሆነብኝ። በታሰርኹበት የጠፈጥሮ ብርሀን አይታይም። አንዲት አምፑል ብቻ ለ24 ሰዓት ትነድ ነበር። የእጅ ሰዓት አልነበረኝም። ታዲያ ዘወትር ገና ከሰዓት በኋላ ሲሆን እኩለ ሌሊት ይምስለኝ ነበር። የማነበው የምጽፍበትም ሆነ የማወራው ሰው በፍጹም አልነበረኝም። አንድ ሰብዓዊ ፍጡር ከራሱ ውጭ ሕሊናውን የሚያሳርፍበት ያስፈልገዋል። ያለዚያ አዕምሮ በጭንቀት በራሱ ውስጥ ይባዝናል። በዝግ ቤት ከመታሰር ይልቅ፣ ግማሽ ደርዘን ጅራፍ ተገርፈው የመረጡ ሰዎችን አውቃለሁ። በብቸኝነት ከቆየሁ በኋላ፣ በጎርኖዬ ካሉት ተባዮች ጋር ሳይቀር ቢጨንቀኝ መወዳጀት ግድ ሆነብኝ። ከቦረሮዎች ጋር ውይይትን ለመፍጠር ተቃረብኩ።”
ብለዋል። እነ መለስ ይኸን የመሰለውን ማሰቃየት የተማሩት ከዚህ የአፓርታይድ እና የኮሙዩኒስት ሥርዓት ነው። የወይዘሪት ብርቱካን እሥራት ግን፣ ከዚህም ይከፋል። በጣም ከባድ ነው። ወንጀሏ የተፈጸመው ዴሞክራሲያዊ ነኝ በሚል መንግስትና ኢትዮጵያውያን ነን በሚሉ አረመኔዎች በውሀ ቀጠነ የተፈጠረ ጭካኔ ነው። እንደነ ኒልሰን ማንዴላ የትግል ልምድ የላትም። በዚያ ላይ የጨቅላ ልጅ እናት ናት። በጾታዋም በዚህ ዓይነት ቆራጥ ትግል ከታዩት ጥቂት ሴቶች አንዷ ስትሆን በከተማ ውስጥ የተገኘች ታጋይ ናት። ሆኖም የነመለስ ግፍ የወለዳት ብርቱ ጅግና ናት።
ታዲያ ይኽ ሁሉ መሆኑ እየታውቀ፣ በውስጥም በውጪም ለሰብዓዊነት ክብር የሚጨነቁ ሁሉ ያለማሰለስ እይጮኹና እየተማጠኑ፣ ያንን ያህል ጊዜ ካሰቃዩአት በኋላ፣ ይቅርታ ጠይቀው መፍታት ሲገባቸው፣ እንደለመዱት በቱኪ ሽማግሌዎች ሽፋን መሰሪ መላቸውን መልለው፣ አማልለውና አባብለው ፈቱአት። ከሁሉም የሚያሳዝነው ግን በእስራት ከተሰቃየችው በበለጠ ጊዜና ቃላት መርጠው ቅስሟን በመስበር የታጋይነቷንና ጥናቷን ለማኮላሸት ያስተላለፉት መግለጫ ነው። ይኸም እራሱን የቻለ የሕሊና ስቃይ ነው።
አሁንም እንኳ ዘጠና ዘጠኝ ነጥብ ስድስት በመቶ (99.6%) አሸነፍን ብለው ብርቱካንን አላመኑአትም። ስሟ ያስፈራቸዋል። በተለይ በሷ ምክኒያት ከአሜሪካም ሆነ ከሌሎች ለጋሽ አገሮች ጋር ስለተፋጠጡና ቢያንስ ብርቱካን ካልተፈታች ዕውቅና እንደሚነሱአቸው ስለነገሩአቸው፣ ሽማግሌዎች ተብዬዎቹን ከጉድ አውጡን በማለት፣ መለስ፣ በተለመደ ሸሩ እንዲሳካለት አደረገ። በዕንቅርት ላይ ጆሮ ድግፍ ማለት ይኸ ነው።የዚያ ሁሉ ስቃይ ደረሰኝ፣ ዋሽተሽ ውጪ ሆነ። ምን ምርጫ አላት? ለማንስ አቤት ትበል?
ብርቱካን በዚህ ሁሉ ኢሰብአዊ ሥቃይ ውስጥ፣ “በይ” የተባለችውን እንድtል ብትገደድ ማን ሊተቻት ይችላል። በግል ድርሻዋ ለመከረኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ እስካሁን ያደረገችው ብቻ ይበቃታል። ይኸ የውሸት መንግሥት ግን፣ ትውልዱን በውሸት ባህል ማበላሸቱ ያሳዝናል። በዚህች ወጣት ሴት ቦታ ሁኖ የደረሰውን ፈተና ለሚመለከት በጣም ከባድ ነው። አራሲቱን ነብር ድመት ሊያደርጓት ተረባርበዋል። እየሱስ እንኳ አምላክነት ሲኖረው “አቤቱ አቤቱ ለምን ትተወኛለህ?” ብሏል። ብርቱካንም የምትመራውን ሕዝብ ለምን ተዋችሁኝ ብትል እና ብትታዘብ ማን ይፈርድባታል። ሕዝቡ በተናጠል ሳይሆን በአንድነት “ሆ” ብሎ ሕዝባዊ ኃይሉን አላሳየም። ወደፊትም ቢሆን፣ ሌላ መፍትሔ ሊኖር አይችልም።
በመሠረቱ፣ ታላቁን ታጋይ ኔልሰን ማንዴላን እንዲፈቱ ግዴታ ለማስገባት በጠየቁአቸው ጊዜ “Prisoners cannot enter into contracts.” – “እስረኞች መዋዋል አይችሉም” እንዳሉት ወይዘሪት ብርቱካንም ይኸን ሁሉ ወያኔያዊ ስቃይ ውስጥ ሁና የፈረምችውም ሆነ የተናገረችው ቢኖር ሕጋዊነት የለውም። ሁሉንም ታሪክ ይፋረዳል። “ብሆር ለልጇ ስትል ተውጋች” ነውና”። በብርቱካን መፈታት ደስ ቢለንም አሁንም ስሟንና ወኔዋን ለመግደል፣ የፈጸሙትና እየፈጸሙት ያሉት ጥቃት ተሰምቶን አንድነታችንን እናጠንክር። እነዚህን መልቲዎች ጊዜ ሳንሰጥ እናሽቀንጥር።
ብርቱካን ምንጊዜም ጀግናችን ናት! እናከብራታለን።

Saturday 2 October 2010

SAMUNA


SAMUNA -

Wednesday 29 September 2010

DIABLOS AND DEDEB


DEDEB AND DIABLOS -

The Priceless Treasure




Priceless Treasure

By Wondimu Mekonnen














Ethiopia!
Holy land biblical,
Ancient nation historical;
Secretive mystical,
Heart throbbing magical;
Paradise typical,
Land of legend classical.
Queen Sheba’s kingdom,
Pioneer of freedom.
Give in to no pressure,
Safe-guard that treasure!
She is a lady so fine,
Your country and mine.
Therefore,
What could one have asked more!
She is a beauty to die for!
Ethiopia!


What a beautiful name!
Ageless amazing fame.
A name written in blood,
Given away for her good.
What a lovely place!
At all times in the space;
People of charming grace,
Blessed land to praise;
A name to mean dark-face,
Long history to trace;
Pride of black race. Green-yellow-red cover,
Adoring tri-colour.
Zion of exiled nation,
Rastaman vibration.
Yeah man! Yeah!
Jah loves in Shashamane!
Dont give in to pressure
Safe-guard that treasure.
Lovely land so fine,
Your sanctuary and mine.
What could one have asked more!
She is a lady to die for!


Ethiopia!

Cradle of mankind,
Home to people from God.
Unblemished purity,
Apex of natural beauty.
Selale massive plains,
Afro-Alpine mountains.
Desert heat tension,
Danakil depression.
Wonders of Rift Valley,
True Garden of Eden;
Soph-Umar Cave of Bale,
Set aside safe heaven.
Jegol labyrinth - Harar;
Fairytale castled Gondar,
Rain forest - Illubabor.
There is no end to wonders,
Abay king of all rivers.
Awash, Gibe, Gennale,
Baro, Wabi-Shebelle.
Dont give in to pressure
Safe-guard that treasure.
Jewel in a shrine,
Your surety and mine.
What could one have asked more!
She is a pearl to die for!




Ethiopia!
Gojam Markos harmony,
Land of milk and honey.
Mighty Ghion Abay,
Green meadow, blue sky.
Lake Tana lies in style,
Thundering fall of Blue Nile.
Love of Alpha-Omega,
Jote gold of Wellega.
Coffee comes from Kaffa,
Arba Minch, Gemu Goffa.
Wollo can boast of beauty,
Music, dance, melody.
Lalibela rock-hewn churches,
Wonders of Architecture.
Tigray has amazing fame,
Heroic past good name;
Pure history - no blame;
Doubters have no more room;
African Jerusalem,
Sacred city of Axum.
South lies Sidamo,
With Awassa Langano.
Arsi tiny wonder,
Shewa the elder sister.
Dont give in to pressure
Safe-guard that treasure.
Together we are fine,
Your destiny and mine.
What could one have asked more!
She is a land to die for!


Ethiopia!



Let my poems pour,
For the beauty I adore.
Endless diversity,
Incredible variety.
Synchronised in unity.
Mosaic of tapestry,
Wild life history.
In the clear blue sky,
Colourful birds fly.
In open lea far away,
Those cheeky monkeys play.
In trees above lagoon,
Booms Galada Baboon.
Home of unique Semein Fox,
Nyala, Walia Ibex.
Land of a multitude,
People with attitude.
At war fighting machine,
In peace polite nation.
Afar the patriotic,
Oromo the athletic;
Anurak-Nuere Nilotic,
Woloye the romantic.
Colourful vest Adare,
Temperamental Tigre.
Kullo-Konta, Gimira.
Gentle farmer Amhara.
Coffee picking Kafficho,
Qotcho pealing Shekacho.
Dorze Haizo weaver,
Wallayta rain dancer;
Kambata hard worker,
Gurage skilled trader..
Hamar, Sidama Hadya, 

















B-e-a-u-t-i-ful Ethiopia!!!!!!!
Her safety has no measure,
Priceless treasure.
Shes only one and all,
Give in to no pressure;
With your life and soul,
Protect that treasure,
Rally around let her shine,
Shes your star and mine.
Any way,
What could one have asked more!
She is the BEST to die for.

READY?

Written in January 1996

Thursday 9 September 2010

ዘመነ ወያኔ - ዘመነ ጨለማ

ከወንድሙ መኰንን፣ በኪንግሀም፣ ጷጉሜን 4 ቀን 2002 ዓ. ም

ወያኔ ኢትዮጵያን ከዘመነ መሳፍንት ወደ ከፋው ዘመነ ዘረኝነት ከወረወራት 19 ዓመት አልፎት ግንቦት ሲመጣ 20ኛውን ሊደፍን እየግሠገሠ ነው። አይ ግንቦት! የማታመጣው ተስቦና ኮሌራ የለ መቸም! ግንቦት 1983 ደኅና አልተገበረም መሰል እንዲህ የከፋብን። በእነዚህ 19 አመታት የደረሰብን እርግማን ጣሊያን ሲወረንም አልደረሰብንም። አንድ የውስጥ መረብ ገጣሚ (internet) ኢትዮጵያዊ አንዴ እንዲህ ብሎ ሲቀኝ አንበብኩ።

እንጀራ በመሶብ፣ ይቀርብ ነበረ
አባሽ በሳህን፣ ትበላው ጀመረ።

ዘመነ ወያኔ ከታሪካዊ ክፋት ሁሉ የከፋ የክፉ-ክፉ ዘመን ነው። የነጻነት ብርሀን ከመቼውም ጊዜ በበለጠ የደበዘዘበት ዘመን ነው። የአገሪቱ ሉዓላዊነት ከመቼውም በበለጠ አደጋ ላይ የወደቀበት ዘመን ነው። ሕዝባችን ከመቼውም ጊዜ በበለጠ የድኅነት አርንቋ ውስጥ የተዘፈቀበት፣ ከሥቃዩ ማምለጫ ጠፍቶት የሚዋዥቅበት፣ አበሳውን ያየበት፣ ተስፋ የቆረጠበት ዘመን ነው። ሕዝባችን በደዌ የተመረዘበት፣ ሕይወት የረከሰበት ዘመን ነው። የወባ ማጥፊያ ድርጅትን፣ ልክ እንደ የአዲስ አበባው የሲሚንቶ ፋብርካ፣ ተነቅሎ ሲዘረፍ፣ የወባ ትንኝ እንኳን ነፍስ እንደገና ዘርታ በአቅሟ ሕዝባችንን እየረፈረፍቸው ነው። ዘመኑ፣ ዘመነ አበሳ ነው። የወያኔ ዘመን “ዘመነ ጨለማ” ነው። ይኸን “አሌ” ብሎ የሚከራከር አዳሜ ካጋጠማችሁ፣ ወይ ከአሰቃዮቹ ፍርፋሪ ለቀማ የደለበ ቅልብ ነው፣ ካልሆነ በጤናው አይደለምና አማኑኤል ውሰዱት። ሆዱ ልቦናውን ያልደፈነበት፣ ጥቅም የሒሊና ዓይኑን ያላሳወረበት ሁሉ ይኸንን በግልጽ እያየ በቁጭት ቆሽቱ ይደብናል።

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሥቃይ መለስ ዜናዊ በኢትዮጵያ ትልቅ የልማት ግብ እንዳስቆጠሩ ያለምንም ሀፍርት ያወሩናል። አንድ ጊዜ ኢትዮጵያ ከዓለም አምስተኛ ፈጣን ዕድገት አስመዘገበች ብለው በየከተማው በገጠገጡአቸው ሙቲቻ (zombie) ኤምባሲዎቻቸው በኩል ውሸታቸውን ረጩት ። ሰሞኑን ሀፍርተ-ቢሱ ዋሾ እንዲሁ ኢትዮጵያ ከ10% በላይ ዕድገት እንዳስመዘገበች በመወትወት አድረቁን። ሀቁ ግን፡ የኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ጠበብት፣ ኢትዮጵያ ከኒዠር ቀጥላ ሁለተኛዋ የመጨረሻ ድኃ መሆኗን የሚያመለክት የምርምር ውጤት ዓለምን አስነብበዋል። ሶማሌ እንኳን ሳትቀር ዘርራን አልፋናለች። 6ኛ ደረጃ ላይ ናት። ጠቅላይ ስቃያችን በ5 ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያ በቴሌፎን እና በኢንተርቴት (የውስጥ መረብ) ከአገሪቱን ማዳረስ አልፈው፣ ወደ ውጪም (export) እንዲሚልኩ ተመጻድቀውብን ነበር። ሰሞኑን ዓለም አቀፍ የውስጥ መረብ ተጠቃሚዎች ማኅበር (International Telecommunications Union (ITU)) መረጃ መሠረት፣ ኢትዮጵያ ከዓለም በኢንተርኔት ስርጭት ከመጨረሻ ሁለተኛዋ ፣ ብሮድ ባንድ የተባለውን ተክኖሎጂ ለማግኘት እጅና እገር የምታስክፍል ናት በማለት እንዴት ወድ እንደሆነ አረጋግጠዋል። ጠቅላይ ስቃያችን እንዳሉት እንኳን አገሩቱን በኢንተርነት ቴክኖሎጂ ማንበሽበሽና፣ ሌሎቹ የፈጥሩትንም የውስጥ መረብ ሕዝባችን እንዳይጠቅም አገደውታል (block አድርገዋል)። ኢቲዮ ሜዲያ፣ ኢትዮሜዲያ ፎረም፣ አዲስ ቮይስ፣ አባይ ሜዲያ፣ ኢትዮጵያን ሪቪው የተባሉ ድረ-ገጾች ኢትዮጵያ ውስጥ አይነበቡም። ኤዲያ! ምናለ እኚህ ግብዝ ሰው ባይመጻደቁብን!

የመለስ ቡድን አዲስ አባባን ከተቆጣጠራት ጊዜ ጀምሮ ድኅነት ድባቡን በአገሪቱ ዘርግቶባታል። ሕዝባችን ከምን ጊዜውም የበለጠ ተራቧል፣ ተጠማቷል፣ ታረዟል፣ ደኽይቷል! እርስብርስ አናቁረውት አነካክሰውታል፣ አበጣብጠውታል። ሰላሙን ነስተውታል። ሕዝባችንን ከፋፍለውት እያፋጁት ነው። አጸደ አምልኮዎቻችን ሳይቀሩ፣ በዘረኞች ካድሬዎች ቁጥጥር ሥር ውለዋል። አገራችን ላይ ዘረኞች ነገሡ። ከሀዲዎች ፈነጩባት። ብሔራዊ ውርደትን አከናነቧት። ሁለቱን ወደቦችዋን ዘጉባት። ግዛቶችዋን ከአንዷ አካል ቆርሰው ያልነበረ አገር ሲፈጥሩ፣ የተቀረውን ለጎረቤት አገር ሸጠውባታል። ሱዳን ለከሀዲዎች ለዋለችላቸው ውለታ ለም መሬታችንን በችሮታ መልክ ተለግሷታል። ምን ይደረግ! ከሀዲዎች አዲስ አበባን ሲቆጣጠሯት እኛ ቤት ለቅሶ ሲሆን፣ ካርቱም ላይ አሸሻ ገዳሜ አልነበር የተደለቀው! ሱዳኖች ይኸ እንደሚሆን ገና ከጠዋቱ ስለተረዱ መጨፍር ይነሳቸው? ወያኔዎች የአገሪቱን ለም የእርሻ መሬቶች ሸንሽነው፣ ባለርስቶቹን ከቄያቸው መንግለው ለባዕድ ቱጃሮች ቸበችበውባታል። ኢትዮጵያን ለመቆጣጠር በታሪኳ ዘመን ሁሉ የተዋደቀች ግብጽ እንኳን ሳትቀር፣ ባለ ሰፊ ቀላድ፣ ባለ ብዙ ጋሻ፣ ባለ ርስት ሆነለች። እናት ኢትዮጵያ ለጠላቶቿ ተመቻችታ፣ ደረቷን ለሞት እንደትገልጥ ተገዳለች! ምነው ታዲያ ይኸ ሁሉ ግፍ ሲፈጸምበት ጀግናውና ቆራጡ ሕዝባችን ግፍን ለመከላከል ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲህ ወኔ ራቀው? ነገሩ ወዲህ ነው። ዘዴው በጣም ረቂቅ ነው። አገሪቱን እንዴት አድርገው፡ እንደጠፈሩአት ምርጫ 2002 አካባቢ የተሸረብቱን ተንኰሎች ብቻ በመዳሰሰ መረዳት ይቻላል።

ቁጥጥር በአገር ቤት

ወያኔዎች ሁለት የመቆጣጠሪያ መሣሪያ አላቸው። ፍርንጆቹ አንዱን ካሮት፣ ሌላውን ዱላ ይሉታሉ። ከሆነ በጥቅማ ጥቅም ማባበል፣ ካልሆን በመጠለዝ ልክ ማስገባት!

ወያኔዎች፣ የአገራችንን ኢኮኖሚ ሙሉ በሙሉ ዘርፈው ከተቆጣጠሩ በኋላ፣ እንዲሁ የሕዝባችንን ሕልውና ተቆጣጥረውታል። ኑሮውን፣ ውሎውን አዳሩን ሙሉ በሙሉ አንቀው ይዘውታል። ድምጽ እንዳያሰማ ጎሮሮውን አንቀውታል። እንዳይሰማ ጆሮውን ድፍነውበታል። አንድ ሰሞን ሬዲዮአቸውን የሚያዳምጥ አልነበረም። የአሜሪካና የጀርመን ድምጽ ሬዶዮዎችን ብቻ ነበር የሚደመጡት። የቻለ “ዲሽ” የሚባል የሳቴላይት ጠላፊ ሳህን ዘርግቶ የውጭ ቴለቪዥን ነበር የሚያየው። በዚህ የተነሳ፣ የወያኔ ጋዜጠኛ የጠነባ መርሀ ግብራቸው ማየት ሕዝቡ እንደትጸየፈባቸውው ገብቶት፣ ዜና ሊያነብ ብቅ ሲል፣ “እንደምን አመሻችሁ፣ ዲሽ የሌላችሁ” ይላል እየተባለ ተቀልዶ ነበር። ዛሬ ያ ቀልድ ቀርቷል። በአገር ቤት፣ ነጻ ሬዲዮ ድሮም አልተፈጠርም ! ነጻ ቴሌቪዢንማ ከቶ ማን አስቦት! ነጻ ጋዜጣን ድራሹን አጥፍተውታል! የተመጣጠን ዕውነተኛ መረጃ ከውጭ ለሕዝባችን እንዳይደርሰው፣ ቪኦኤ (የአሜሪካን ድምጽ ሬዲዮ) ዛሬ የለ! ጀርመን ድምጽ ዛሬ የለ! ኢሳት ቴሌቪዥንማ፣ ሳተላየት እንዴት ማፈን እንደሚቻል የአፋኝ ተክኖሎጂ መለማመጃ ሁኗል። “የቻይናን” የፍቅር ዕድሜ ያሳጥርልንና በአጭሩ ተሰምቶ በማይታወቅ ቴክኖሎጂ ከአየር ላይ ቀልበውታል። ይኸ ማለት ሕዝባችን መጮህ ቀርቶ ከውጭ የምንጮለትን እንኳን እንዳይሰማ ምንም ዓይነት መረጃ እንዳይደርሰው ቀፍድደው ይዘውታል። እእንዳይዘዋውር፣ እግሮችን ጠፍረው አስረውታል። በአገሩ እንደድሮው ከቦታ ቦታ ተዘዋውሮ አርሶ አምርቶ፣ ነግዶ አትርፎ እንዳይበላ ከልክለውታል።
ሕዝቡን በወረዳና በቀበሌ ከፋፍለው ከመቆጣጠር አልፈው፣ ጎጥና ጋሬ በመባል ሥርዓት (system) ታች ወርደው እስከ አምስት ሰው ድረስ የሚቆጣጠሩበት ሕዋስ ፈጥረዋል። በዚህ ክትትል መሠረት፣ ማንም ዜጋ፣ ለምሳሌ ገብሬ፣ ከተወሰነለት ሁኔታ የማፈንገጥ ምልክት ካሳየ፣ ለዘር ብድር ከባንክ አያገኝም፣ ማዳበሪያ በብድር አይሸጥለትም፣ ከውጭ በልመና የመጣውን የዕርዳታ እህል እንኳን አያገኝም። ማንኛውም ዜጋ ጥቅም ማገኘት ከፈለገ፣ የአባልነት ፎርም መሞላት አለበት።

ይኸን ፎርም ያልሞላ ተማሪ፣ ዩኒቨርሰቲ የመግባት ዕድል የለውም። ይኸን ፎርም ያለሞላ ተመራቂ የሥራ ዕድል የለውም። ይኸን ፎርም ጎጡና ጋሬው በሚያዘው መሰረት ያልሞላ ዜጋ ኢትዮጵያ ውስጥ ሕይወት የለውም። ያለው ምርጫ መሰደድ ነው። ለዚህ ነው ወጣቶቻችንን በርሀ የሚበላቸው። ባሕር የሚያሰምጣቸው። የሶማሌ መንገድ መሪዎች የሚያርዱአቸው። አንድ ሰው ይኸን ፎርም ሞላ ማለት ደግሞ፣ እሱም እንደነሱ ወየነ ማለት ነው። ምርጫ 2002ን በ99.6% አሸነፍን የሚሉት አንዱ ዜዴአቸው እንዲህ ዓይነቱን ፎርም በማስሞላት ነበር። እዚህ ቦታ ስለሚያጠብብን ነው እንጂ ሌላም ለምርጫው የተጠቀሙበት ፎርም አለ። እነሱ ምርጫውን እጃቸው አስገብተው ያበቁት ገና በ2000 ዓ ም የክልል ምርጫ ብቻቸውን ሩጠው ብቻቸው ያሸነፉ ጊዜ ነበር። “ኢህአዴግን እመርጣለሁ” የሚል ፎርም እያንዳንዱን ተራ ዜጋ አስፈርመው ይዘው 2002ን ይጠባበቁ ነበር። አልፈርምም የሚል ዜጋ ያው ከተቃዋሚው ጎራ ተፈርጆ ይቀመጣል። ተወዳዳሪ ከሆንም አርፎ እንዲቀመጥ በጋሬው በኵል መልዕክት ይደርሰውል፣ እምቢ ካለም እስከመገደል ይደርሳል። ሲገደል ደግሞ ታፔላ ይለጠፍለታል። ለምሳሌ የደቡቧን ተወዳዳሪ ባለትዳር ወይዘሮ ከገደሏት በኋላ፣ የድብቅ ፍቅረኛዋ እንደገደላት በቪኦኤ ሳይሰቀጥጣቸው ተናግረዋል። የኦብኮውን ተወዳዳሪ ከገደሉ በኋላ “አባላችን ነበረ። ኮሌራ ገደለው” ብለው ዐይናቸውን በጨው አጥበው ድርቅ ብለው ዋሽተውናል። ኮሌራ ማለታቸውስ ባልከፋ፣ ከነሱ የባሰ ኮሌራ የለምና፣ አባላችን ነበር ማለታቸው ግን አብጋኝ ውሸት ነበር። ይኸ እንግዲህ ዱላው መሆኑ ነው።

ምርጫ 2002 ሲደርስ ወያኔ በሚያስገርም ሁኔታ ገንዘብ ይረጭ ነበር። ገንዘቡን እንደ አቧራ አብንነውታል። የሚገርመው ነገር፣ በየደቦው (በየወንፈሉ)፣ በየዕድሩ፣ በየዕቁቡ፣ በየለቅሶው፣ በየገቢያው እየተዘዋወሩ፣ የሰውን የግል መርሀግብር ወይም ዝግጀት (programme) ሳይስፈቅዱ፣ እየረገጡ፣ “ኢሕአዴግን ምረጡ” እያሉ ከመደስኮርም አልፈው፣ ብር፣ ካናቴራ፣ ሹራብ እና ሰዓት ድረስ ለየአንዳንዱ ለተገኘ ሕዝብ በስጦታ መልክ ችረውታል።

በጄ የገባው ሰዓት የተቸረው በአንድ ሠርግ ላይ ነው። ሶስት መቶ ዕድምተኞችና 5 ያልታጋበዙ የወያኔ በር ሰባሪዎች (gate crushers) ነበሩ:: እንግዶቹ እየበሉና እየጠጡ እየተዝናኑ፣ ሙዚቀኞቹ እየዘፈኑ፣ ሚዜዎቹ እስክስታ እየመቱ ሳለ፣ ባለጌዎቹ የወያኔ ካድሬዎች በቀጥታ ወደ መድረኩ ወጥተው ድምጽ ማጉያውን ነጥቀው ተቆጣጠሩት። ነገሩ በጣም የሚያናድድ ቢሆንም፣ የሙሽርቹ ወላጆችም ሆኑ፣ ሚዜዎች፣ ወይም እድምተኛው፣ ባለጊዜዎች መሆናቸውን እንደተረዱ ጸጥ ብሎ ከማዳመጥ ባሻገር አንዳችም ምርጫ አልነበራቸውም። እጅ እጅ የሚለውን የቆረፈደ የ“ኢሕአዴግ” መጪው የ5 ዓመት መመሪያ (Policy) ያሉታን አብራሩ። በደሞክራሲ ዕደገት፣ በኢኮኖሚ ምጥቀት፣ በሳይንስ ብስለት፣ በቴክኖሎጂ እምርታ፣ ተቅደጀ የሚሉቱን ወሬ ዘበዘቡ። እድምተኛው ችክ እያለው ሰማቸው። በኋላም ላይ፣ ይኸንን ሰዓት አውጥተው ለያንዳኑ ዕድምተኛ በተኑት። ሳዓቱን ትኵር ብላችሁ ብታዩት፣ ወርቃማ ነው። ከመክበዱ በስተቀር በጥሩ እጅ የተሰራ ነው። ወርቃማ ወለሉ ላይ (dashboard) “መጪው ጊዜ ከኢህአዴግ ጋር ብሩሕ ነው” የሚል ዐርፍተ ነገር ተጽፎበታል። ድንቄም! እንዲህ አድርጎ ብሩህ ጊዜ ሰመጣ አይተንም ሰምተንም አናውቅም! ለማንኛውም፣ ዕድምተኛው ወርቁን ተቀብሎ “ኢሕአዴግን እመርጣለሁ” ብሎ ፈርሞ ሸኛቸው። ግልግል!
ምርጫ 2002 እንግዲህ በዝህ ሁኔታ ነበር 99.6% ድል ለወያኔ ያመቻቸው። ይኽቺ ናት ዲሞክራሲ! ይኽቺ ናት ጨዋታ! መጪው አምስት ዓመትም ሆነ፣ ከእንግዲህ ወዲያ ወያኔ ሥልጣን ላይ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚቆይባት ግዜ ዘመንም ይሁን አመታት፣ ወራትም ይሁኑ ሳምንታት፣ ቀናትም ይሁኑ ሰዓታት፣ ዲቂቃም ይሁን ሰኮንድ፣ ለሕዝባችን የድቅድቅ የጨለማ ዘመን ነው። የጨላማ ዘመንነቱ ድግሞ፣ የብሒል ብቻ ሳይሆን የጥሬ ቃሉም ጭምር ነው። አዲስ አበባ ኢሌክትርክ አጥታ በወያኔ ዘመን ጨላማ ውስጥ ተዱላ አበሳዋን እየገፋች አይደል!

ውጭ-አገር ኗሪውን ለመቆጣጠር የተየቀሰ ዘዴ

ከዚህ በፊት ብዙ ብለናል። አዲስ ነገር ስላለ አሁንም እንላለን። ወያኔ የአገር ቤቱን ሕዝብ ሙሉ ለሙሉ ተቆጣጥሮ አብቅቶለታል። አሁን አንደኛውን ፊቱን ወደ ውጭ አገር አዙሯል። በ2006 የዘረጋውን 52 ገጽ መመሪያ አሁን አሻሽሎት እንደድሮው አምባሳደሮቹ የሚመሩት ሳይሆን በቀጥታ ከአዲስ አበባ “በደኅንነት እና በስለላ መሥሪያ ቤት” የሚመራ ቡድን ተቋቁመዋል። ዕቅዱንም ከ2002 ዓ.ም ጀምሮ ሥራ ላይ አውሏል።
ሥራቸው መረጃ መሰብሰብ ብቻ አይደለም። ከዚያ የላቀ ነው። ብዙ ሃላፊነት ተጥሎበታል። አምባሳደሩ አፍንጫው ሥር የሚደረገውን እንዲህ ዓይነቱን ሥራ ጨርሶ የማወቅ መብት የለውም። የስደተኞችን እንቅስቃሴ ከመከታተል ባሻገር፣ በተለያየ የቁጥጥር ዘዴ ፈልስፎ ደንበኛ መመሪያ ወጥቶ መጠቀም ጀምረዋል። ልዩ ስውር ካሜራ ይዘው በተልያዩ የሕብረተሰቡ ስብሰባ ላይ በመገኘት ይቀዳሉ። በሕብረተሰብ ማኅበራት አመራር ውስጥ የራሳቸውን ሰዎች አሰርገው ማስግባት ይሞክራሉ።

ባለፈው ዓመት ከተጀመሩት ዜዴዎች አንዱ፣ የስደተኛውን ኪስ የሚያራቁቱበትን ብልሀት መፍጠር ነበር። ስደተኛው አገር ቤት ንዋይ እንዲያፈስ የሚደረገው ጥረት በተለያየ መንገድ ይቀጥላል። አሁን ገንዘብ በውጭ ምንዛሪ አገር ቤት ባንኮች ውስጥ ማስቀመጥ እንደሚቻል፣ ለማግባባት ፎርሙን ካድሬዎቹ እየበተኑት ደርሰንበት ከዚህ በፊት ኅብረተሰባችንን አስጠንቅቀናል ። አገር ቤት ሂዶ መኖሪያ ቤቱን እንዲሠራ የሚሰጠው የመሬት ምሪት ድልላ አሁንም በተሻሻለ መንገድ ይቀጥላል። መሬት እመራለሁ ብሎ መረባቸው ውስጥ ጥልቅ ይልላቸዋል። ይኸንን የስለላ መረብ እንዲመራ ከኢትዮጵያ ታዞ የመጣ በለሥጣን ወይንም በሚኒስተር ደረጃ፣ ካውንስለር ተብሎ በየአገሩ ትሹሟል። ካልሆነም በአንደኛ ጸሐፊንት ደርጃ ይቀመጣል። ለምሳሌ በሎንደን የሚከተሉትን ሦስት ስሞች ልብ ብላችሁ አስተውሉ። ሰላዩን እናንተው አውጥታችሁ አውርዳችሁ አሰላስላችሁ ድረሱበት። (ስሙም ሰላይ ነኝ እያለ ይናገራል።)

ብርሀኑ ከበደ - አምባሳደርና (ለስሙ) ባለሙሉ ሥልጣን (His Excellency Ambassador Berhanu Kebede)
ሀብቶም አብራሀ - ሚኒስቴር ካውንስለር (እ-እ-እ-ም! ይቅርታ ጉሮሮየን ከርክሮኝ ነው) (Habtom Abraha - Minister Counsellor)
ተስፋየ ይታይኽ - አንደኛ ጸሐፊ (Tesfaye Yetayeh - 1st Secretary - Community Affairs)

ለመሆኑ የኮምዩኒቲ ጉዳይ ተከታታዩ የትኛውን ኮሙኒቲ ጉዳይ ሊያስፈጽም ነው እዚያ የተጎለተው? ለመሆኑ ከራሱ ኮሙዩኒቲ ወይም ማኅበርሰብ ጋር የተጣላ ኤምባሲ፣ ምን ዓይነት ኮሙይኒቲ አለኝ ብሎ ያወራል? ለማንኛውም ምለመላው ቀጥሏል። ዓላማቸው ብዙ ነው። ዋናው ንጹህ ዜጋ በመምሰል ኢትዮጵያዊ የሆነውን ተቋም ሠርገው በመግባት ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር ነው። እዚህ ላይ ቤተክርስቲያናችንም ዒላማቸው ውስጥ አለችበት። የኢትዮጵያ ማኅበረሰባት ድርጅቶች ሙሉ በሙሉ ዒላማ ውስጥ ናቸው። እንግዲህ ፍርጀ ብዙውን በጥቅሉ በሁለት መክፈል እንችላለን። እንሱም ማደራጀትና መንጠቅ ናቸው። ማደራጀቱን ቀጥለውበታል። ማደራጀትን በተመለከተ ወያኔ የሚመራው “የኢትዮጵያ ማኅበረስብ” በየኤምባሰው ቅጥር ገቢ ይቋቋማል። በሎንደን፣ ለምሳሌ ሆዳደር “ያለው” የሚመራው “ይሁንታ” በመባል የሚታወቀው ዓይነት ማለት ነው። የየብሔረሰቡ የልማት ማኅበር እየተባለም የስለላ መዋቀሩ በተለየ መልኩ አደረጅቶ ሊቆጣጠረው እየሞከረ ነው። ጥሩ ምሳሌ የሚሆነው ሜይ 29 ቀን 2010 በሎንደን “አማራ ልማት ማኅበር ” ብለው የጠሩት ነው። መልማዮቹ ወይ ለዚሁ ጉዳይ ከአዲስ አበባ፣ አዲስ የተሰደዱ አስመሳይ ስደተኞች ሊሆኑ ይችላሉ፣ ካልሆነም ነባር የባሰባቸው ሆዳሞች አሉበት። ወጣቱን “ስፖርት ከበብ አቋቋመንልሀል፣ እናደራጅህ” በማለት ይቀርቡታል። ምግብ፣ ለስላሳ መጠጥ፣ አንዳንዴም ሙዚቃና ዳንኪራ በነጻ ያቀርቡለታል። ዋናው ነገር፣ የወያኔ አምባሻ ምልክት ባንዲራ ያለበት ካናቴራ ልብስ/ልብሺ ማለት ደረጃ ላይ ሲደርሱ ይነቃባቸዋል። ባለንግድ ድርቶችም፣ በተለያየ ጥቅማ ጥቅም ሊያዙ ዕቅድ ውስጥ ናቸው። ውጭ ለምንኖረው ለያንዳንዳችን አንዳንድ ዕቅድ ነድፈውልናል።

በተለያየ ምክንያት ኤምባሲ የረገጠ ማንኛውም ሰው አድራሻውን፣ ስልክ ቁጥሩ፣ ኢሜሉ ይወሰዳል። ያ ዳታ ቤዝ (database) ውስጥ ይገባል። ወያኔ ያንን መረጃ እንደሁኔታው ጥቅም ላይ ያውለዋል። ለምሳሌ፣ ስማችሁን፣ አድራሻችሁን እና ኢሜላችሁን ለወያኔ የሰጣችሁ ካላችሁ እንደሚከተለው ዓይነት መልዕክት ይደርሳችሁአል። ቀጥሎ የምታነቡት ዕውነተኛ ከወያኔ የደረሰ መልዕክት ነው።

Date: Jul 14, 2010 10:47 AM
Subject: Opportunities in Ethiopia
To: " >
Representatives from capacity building minister will be coming to US in less than a month.
They will be looking for skillful and professional Ethiopians willing to work in Ethiopia.
Specific areas of interest include Agriculture, Medicine, IT, Law, Finance, and Economics.

I am planning to set up a meeting with these representatives. If you are interested, please fill out the below information and send it to me.

Name::__________________________________________________________
Residence City/Country:____________________________________________
Phone: __________________________________________________________
E-mail: __________________________________________________________
Citizenship: ______________________________________________________
Education: ______________________________________________________
Qualification (Knowledge/Skill/Ability): _______________________________
Specialization: ___________________________________________________
Experience: _____________________________________________________
Desired Position/Service: __________________________________________
Availability Type: ________________________________________________
(permanent employment, temporary/term employment, consulting, volunteer, etc..)
Availability Period: _______________________________________________
Desired Location: ________________________________________________
Desired Salary/Compensation: ______________________________________
Desired Benefit: _________________________________________________
Supplemental Documents (Resume, CV, etc..): ________________________
Additional Information: __________________________________________
________________________________________________________________
ዕውነት ኤክስፐርት ፈለገው እንዳይመስላችሁ። ኢትዮጵያ በሥራ አጦች ተጨናንቃለች። ዓላማው “አገሬን እረዳለሁ” ብላችሁ ስትቀርቡት፣ ሕይወታችሁን ቁጥጥር ሥር ሊያውላችሁ ነው። ቀጥሎ የጠነባ ፖሊቲካውን ሳትወዱ በግዱ ሊግታችሁ!
ሌላው ሥራ የሚከተለው ነው። ጠቅላይ ሥቃይ መለስ ዜናዊ ውጭ አገር በጎበኙ ቁጥር፣ ስደተኛው ሰላማዊ ሰልፍ እየወጣ ቁም ስቅላቸውን ሲያሳያቸው ኑሯል። ያ መቆም አለበት። ለምሳሌ ጂ-20 በተባለው ስብስባ ላይ ሊገኙ ሎንዶን ሲመጡ ከአውሮፓ ተሰባስበው በመጡት ኢትዮጵያውያን ቆሌአቸው ተገፎ የርእስ በሔሮች መሳለቂያ መሆናቸው አናዶአቸዋል። መኪና ውስጥ ገብተው የተተኮሶባት ድኩላ መስለው ተደናግጠው ሹክክ ሲሉ አንዱ ወንድማችን ፎት አንስቶአቸው እነሆ እስከዛሬ ምስላቸው እንደጉድ፣ ለጉድ ይታያል። መሬት ያደሉት፣ የሁለተኛ ዜግነት መብት ልዩ ምልክት የሆነውን የኢትዮጵያዊነት ካርድ በ£400 ያስገዙአቸው ስደተኞች እንዳሸን በፈሉባት ሎንዶን ውስጥ እንደዚህ ዓይነት ውርደት ለመመከት ብርሀኑ ከበደ ደጋፊዎቻችውን ባለማሰማራታቸው ቁጣ ብጤ እንዳወረዱባቸው ሰምተናል። ዴንማርክም፣ እንዲሁ ዘምተንባቸው ነበር። ኦቶዋም ተመሳሳይ ዕድል ገጥሞአቸዋል። ዋሽንገንም አልቀረላቸውም። ታዲያ ለዚህ ዓይነቱ ተግባር አንድ ነገር መደረግ እንዳለበት በማምን በየአገሩ ያንን የሚከታተል ግብረ ሀይል ተቋቅሟል። ሥራም ጀምሯል። መፍትሔው ቀላል ነው። የወያኔ የድጋፍ ኮሚቴ በየአገሩ በገንዘብም ሆነ ባገኙት ዕድል አቋቁመው በየጊዜው አጽፋ ሰላማዊ ሰልፍ እያደረጉ “ኢሕአዴግ ለዘልዓለም የኑር” የሚሉ በቀቀኖችን (parrots) መፍጠር ነው። ይኸንን ኦታዋ ካናዳ ላይ ለማድረግ ሞክረው ነበር። አሁን በነሐሴ ሆድ-አደር ጋዜጠኛ ንጉሤ ወ/ማርያምና፣ ግንባሩ ላይ ብር ከተለጠፉለት መላጣውን “ጸጉሩ ሞላ ያለ” ብሎ ከማሞገስ ያማይመለስ ሒሊና ቢስ ዘፋኝ ሰሎሞን ተካልኝ ጋር ያዘጋጁት የወያኔ ድጋፍ ሰላማዊ ሰልፍ የዚያ እንቅስቃሴ አንዱ አካል መሆኑ ነው ። ዓባይን አስታከው “ከመለስ ጋር ወደፊት! ወያኔ የልጅ ልጅህን ይገዛል።” ብለው ላንቃቸው እስኪደርቅ ጩኸው ተመለሱ። ሰሎሞን ተከልኝም “ቅንድቡ ያማረው” የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሥቃይ “ለዘልዓለም ይግዛን” ብሎ ዘፍነላቸው። ምን ችግር አለው፣ አላሙድ የተባለው ቱጃር ትንሽ ቀርሺ ድግሞ ቢለጥፍለት፣ ድንክየውን ጠቅላይ ሥቃይ “መለሎው መለስ” ብሎ ቢዘፍን ሊደንቀን አይችልም።

የኢትዮጵያ ፈርስቱ (Ethiopia First postmaster) ብንያም፣ “ለጋዜጠኛ” ንጉሤ ወ/ማርያም ደርሶ ያነበበውን የፍቅር ደብዳቤ ሰምታችሁአል። እንዲያው ካልሰማችሁ፣ በሞቴ በግርጌው በተጠቀሰው አድራሽ ጠንቁላችሁ ስሙት ። እኔ መቸም ኢትዮጵያ ውስጥ የወንድ ለወንድ ፍቅር ግሎ እንዲህ አደባባይ ሲወጣ ገና ማየቴ ነው። ሴትና ወንዱም ቢሆን በድብቅ ነበር።

ወይ ፍቅር እያለ ሰው ያወካል
ግን አንድም ሰው አላየው ቁሞ በአካል

በሎ ዘፈነ መሀሙድ! ብንያም ንጉሤን እንዴት መጥራት እንዳለበት ግራ ተጋብቶ አንዴ ንጉሥዬ እያለ ሊያቆላምጠው (ንጉሤ ድግሞ ለማቆአላመጥ አያመች ጣጣ) ሲሞክር፣ በሌላ ጊዜ ንግስቲየ እያለ ፍቅሩን ለገልጥለት ሲሞክር ለሰማ “ይኸስ ብሶበታል! ጾታም መለየት አቅቶታል” ያሰኛል። ብንያም ከመጀመሪያም የወያኔ ቫይረስ ተሸካሚ ሆኖ አሁን እንደአላሙዲ የባነነበት ዜጋ ሊሆን ይችላል። ንጉሤ ወልደማርያም ግን፣ ለሆዱ ያደረ ሆዳም ነው። እንደሰማነው ከሆነ፣ ወያኔ ገርፎት ሲያባርረው፣ ዘረኞቹን ይኮነነን እንደነበረ ጓደኞቹ ይነግሩናል። ዛሬ 180% ድግሬ ዙሮ የወያኔ አንድ ቁጥር አፈቀላጤ ያደረገው ያው ከርሱ መሆን አለበት። ቆይ ብቻ! ወያኔ የንጉሤ ወልደማሪያምን ጎተራ ሆድ ከሞላ፣ የወያኔ ሰልፍ ድጋፍ ቢያዘጋጅ፣ ምን ያስደንቃል? ብዙ ንጉሤዎች በየከተማው ሞልተዋል። እንዲሁ እንደጨለመብን የምንቀር መስሎአቸዋል ይዘባነኑብናል። አይነጋ መስሏቸዋል።

እንዲህ ዳምኖ ዳምኖ የዘነበ እንደሆን
የጎርፉ መሄጃ በየት በኩል ይሆን
እንዲ ጢሶ ጢሶ የነደደ እንደሆን
ያመዱ ማፍሰሻ በየት በኵል ይሆን?

ስደተኛው ጓዴ! ይኽች ክፉ ዘመን እንደከፋችብን አትቀርም፡ ታልፋለች! በነዚህ የወያኔ ልክፍተኞች በሰደት በምትኖርበት አገር ተሳስተህ ትቀርባቸውና፣ ዋ! በወያኔ ልክፍት እንዳትለከፍ ሁልጊዜ እራስህን ጠብቅ። እስካሁን መድኀኒት አልተገኘለትም። አንድ ቀን ለነዚህ ኃጢአተኞች የሚመጣው መዐት አንተንም ይዞ እንዳይነጉድ አንተነትህን አድን። ዘመነ ጨለማን በዘዴ ዕለፈው! በተረፈ እግዚአብሐር፣ የኢትዮጵያ አምላክ፣ ሁላችንንም በያለንበት ጠብቆን ብርሀኑን ያብራልን።

Wednesday 8 September 2010

Palace-based liars and swindlers

December 3rd, 2009 No Comments

By Wondimu Mekonnen

Among so many negative qualifications the Weyane gang has accumulated through the years, their mastery of lies stand out as the most blatant. For Weyane, lying is a habit engrained deeply with its nature. Probably no one had told them when they were still kids that lying is a mortal sin. The Meles regime does not blink when it lies and looks back in your eyes without any shame. Their arrogance and lack of decency is such that they don’t even bother to cover their most outrageous lies. It is an open secret that no one taught them ethics in governance of a country while they were in the bush, but at least the moral values they had to learn from their parents could have enabled them to distinguish right from wrong. As a lady this writer is acquainted with once said: “They came from the bush therefore they always act wild.”

Geoffrey York, in his article “Ethiopia: Land of silence and starvation” wrote on Globe and Mail, Canada, on November 7, 2009 the following:

A famine is growing across Ethiopia, but the government is clamping down on information – even ejecting aid agencies that could help bring aid for fear of provoking unrest and losing their grip on power.1


The regime may deny the glaring facts, but the pictures speak different stories. Millions are daily falling like autumn leaves but the dictatorial regime in Ethiopia denies the existence of famine in Ethiopia. They would tell you unashamedly “there is hunger but there is no famine.”
Ethiopia had been poorer and poorer but the magnitude of poverty during the Woyyane reign is incomparable to any in the past history. The 1973/1974 famine killed about 200,000 people. That 1984/85 famine killed 900,000 people2. It is worth to mention here with reference to the 1984/85 famine that the rebels that are now in government were fighting the Dergue regime in those days. After blocking relief distribution routes, the rebels offered their services to the international donors to distribute food to refugees from Tigray sheltering in the Sudan and those living in territories under their control. According to Gebremedhin Araya, one of the former members of TPLF and in charge of their financial affairs, the current regime also cashed on that famine in billions of dollars3. The TPLF swindled billions of cash out of unsuspecting kind-hearted Western donors by posing as concerned members of Tigray nationalists that would distribute the aid fairly to the needy but the poor did not see any penny from that money. In his private e-mail exchange with this writer, one of the top former rebel leaders, who is now in exile wrote:

“What I am sure of is that the Meles/Sebhat group was buying the same sacks of grain over and over again by using fighters like Gebremedhin Arya, pretending as merchants. Neither the grain nor the cash reached the victims of famine. What you might read in the booklet “Tigray: Ethiopia’s Untold Story’ by Max Peberdy, 1985 with Gebremedhin’s picture receiving the money from a foreigner/donor and the other fighter taking the grain was a true tragic drama how this gang was snatching relief aid from the hungry people.”
Now, these are the same people who claim to be caring and in charge of a country with a very religious heritage and distinguished high sense of moral values. Swindlers are in power and still they are swindling billions of aid money to this day.

These days, the entire country is exposed to catastrophic famine. Now over 13 million people are exposed to famine, including 6.5 million people on food safety net. Those areas that had never gone hungry in the past are now devastated. There is crop failure everywhere. Loggers have cut down forests and left the land barren. Loggers and commercial farmers, for example, destroyed rainforests in a place called Gamadiro, in Sheka Zone. The biblical time famine is catching the whole country like a wild fire, but our leaders tell us that the economy is booming. Well, there may be some truth when it comes to their personal fortunes. They own the country now. There is indeed “economic growth” but the growth doesn’t reach the people as it is TPLF’s companies that never pay taxes and bank loans and its foreign and local partners that are taking the lions’ share, while the people face silent death in every corner of the country. The blood sucking TPLF elite and their cronies are indeed fattening while the majority are starving en masse.

Government corruption in Ethiopia is rampant. They make money by selling everything that comes into their possession, including the fertile lands in the country. The land was nationalised during the Dergue era. The Tigray People’s Liberation Front, that is ruling Ethiopia disguised as EPRDF at the same time swearing in the name of “market economy” retained the nationalised land in its grips. Farmers have to be loyal to the regime, if they wanted to have a land to farm on. And yet, TPLF has turned fertile arable lands into cash commodities. Where does all the money go? Surely, not into the pockets of the starving people of Ethiopia!

Stephanie McCrummen of the Washington Post wrote on 28 November 20094 in her article, Ethiopia being ‘used like an empty womb:

“In recent months, the Ethiopian Government began marketing abroad one of the hottest commodities in an increasingly crowded and hungry world: farmland.
”Why attractive?” reads one glossy poster with photos of green fields and a map outlining swathes of the country available at bargain-basement prices. ”Vast, fertile, irrigable land at low rent. Abundant water resources. Cheap labour. Warmest hospitality.”
So, the swindlers are amassing billions of dollars on one hand from proceeds of farmland sales while on the other hand denying the existence of famine in the country. Lying, cheating and swindling were something they learned while they were still in the bush but the trouble is they have been keeping it up as bad habits die hard even after becoming in charge of the government for the last 18 years.

The regime keeps on speaking of continuous development without blinking while on the ground millions go about with empty stomach. May be their own pockets have swollen but in reality the people on the street are poorer than ever. These days, Ethiopians who visit Europe and the USA to see their family members in exile are so surprised to see their relatives watching Ethiopian television via satellite, because they have stopped watching it in Addis Ababa and other main cities. When asked, why, they would simply say that they are fade up with listening to empty tyrant regime’s propaganda and pack of lies for the last 18 years and they have had enough. Addis Ababa is poverty-stricken. People are dying of hunger, but members of ruling elite are partying at the Sheraton and the Hilton all night long at the expense of the dying multitude. Inflation is rampant. Unemployment is at its highest pick. The city that had never experienced power shortage during the past governments, blackout is common place. And yet, the regime claims growth. Provably they must be misreading poverty growth as economic growth or they must be hallucinating by simply looking at their own swollen wallets.

One amazing claim was made recently via a communiqué released by the Embassies to its constituents throughout the cities of the World5. Uncut, it reads follows:

From: constituentcyinfo 
Sent: Wed, Nov 25, 2009 11:27 am
Subject: Ethiopia will be 5th Fastest Growing Economy in the World in 2010
-The Economist predicts Ethiopia’s economy will grow by 7 per cent in 2010. It also estimates inflation will be reduced by 12 per cent.

According to information posted in its website, it also said Ethiopia has become five top fastest growing economies in the world.

The prediction is close to Ethiopia’s plan which anticipates increasing its economic growth by over 10 per cent and reducing inflation below 10 per cent in 2010.

The magazine predicts Qatar to top the fastest growing economies in the world with a GDP growth of 24.5per cent followed by China, Congo (Brazzaville), Turkmenistan and Ethiopia.

Ethiopia’s GDP is expected to reach 35 Billion USD in 2010 and inflation is estimated at 12 per cent. Kenya which is the biggest economy in East Africa is predicted to have a GDP of 38 Billion USD in 2010.

It said if Ethiopia’s GDP growth forecast is accurate, Ethiopia could soon surpass Kenya, to become East Africa’s biggest economy.

Opening the joint session of the House of Peoples’ Representatives and the House of the Federation, President Girma Woldegiorgis had said the Ethiopian government will be exerting utmost efforts to register more than 10 percent annual economic growth and control inflation at less than 10 percent during the 2002 E.C.

The magazine also predicts Ethiopia’s economy to grow by 7 per cent in 2010 and inflation estimated at 12 per cent.

It also indicated that rapid development in the agriculture sector significantly contributed in the economic growth of the country.
Various websites have set up blogs to discuss on causes of rapid development
A former career diplomat who now lives in exile who saw the lies repeated at Sudan Tribune website6 said with disgust:

“It appears that the Chinese had given them thousands of calculators, so they exercise some math with them. As a result they found that by adding as many zero as possible in aggregate the two thousand calculators in Melese’s office manage to work out the Ethiopian GDP growth at 35 billion. The results from other gang member’s calculators are not yet in. However the final figure is estimated to be about 1.3 trillion. The Chinese, the World Bank, IMF, EU are happy for the excellent use of calculators made by the Meles brain trust. It seems that they will be sending their ministers of finance, and high executives for training to Addis Ababa. This is a very serious joke, keep crying”
A very senior journalist at BBC who saw the news at the same website and said:

“Interesting! That’s the way to get publicity, eh?”
These guys, who have been swindling all their lives, have no shame at all. Any decent government living off begging from donor countries would have had the decency to admit that the country had been economically poor in the past and it has become poorer now and therefore should ask for more help to get out of the vicious circle rather than ridiculing itself.

Of course, we know that members of the ruling regime are stinking rich. The Prime Minister’s wife is said to be a mega billionaire though she attempted to put on a brilliant act last year7. As she is now in control of the EFFORT business empire, her hands are in every casher’s till.

We know they are lying. They know they are lying. They know that we know they are lying. The world community knows that Ethiopia is poorer than ever. Who are these lords of poverty and conmen trying to fool? In fact, no one but themselves!
Ref;

1 www.theglobeandmail.com
2 www.scaruffi.com/politics/disaster.html
3 www.ethiomedia.com/course/4306.html
4 www.smh.com.au
5You can see how that constituency was built by clicking at: http://www.ethiomedia.com/carepress/attack_on_diaspora.html
6 http://www.sudantribune.com/spip.php?article33292
7 http://www.youtube.com/watch?v=gmEmryaheLk

የወያኔ ሸረሪት ድሯን ታደራለች፣

ወንድሙ መኰንን፣ ሎንደን 10 June 2010

ሰሞኑን አንድ ቀልድ ከኢትዮጵያ መጥቶ በየድረ-ግጹ እየተዘዋወረ ነው። ቀልዱም እንዲህ ይላል።
ልዑል እግዚአብሔር ሆይ! ባለፈው ዓመት፡ ዘጠና ዘጠኙ ከመቶ ሕዝባችን የሚወዳቸውን፡

1ኛ. ዝነኛውን ዘፋኛችንን፣ ጥላሁን ገሠሠን ወሰድክብን
2ኛ. ዝኘኛውን ተዋናይ፣ ሲራክ ታደሰን ወሰድክብን
3ኛ. ዝነኛውን ቀልደኛ አዝናኝ፣ተስፋዬ ካሳን ወሰድክብን
የዘንደሮው ዝነኛው ተወደጁ ፖሊቲከኛችን ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ዜናዊ ናቸው።

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሥቃይ፣ መለስ ዜናዊ 99.6% በምርጫ አሸነፍኩ የሚለውን አዋጃቸውን ተከትሎ ነበር ይኸ በአዲስ አበባዎቹ የአራዳ ልጆች የተፌዘው። ተወዳጅ ተወዳጁን እየመረጠ ጌታ ከወሰደ አሁንም ፈቃዱ ይፈጸም። አሜን እንበል። አሜን!
የወያኔ እጅ፣ አገር ቤት ያለውን ሕዝብና ተቋሙን ተቆጣጥሮ የመደምሰስ ስትራተጂው (የረጅም ግብ ዕቅዱ) ቀፍድዶ ይዞ ዓላማው ሙሉ በሙሉ የተሳካለት ይመስላል። ያልተቆጣጠረው አንዳችም ነገር የለም። ያ ሁሉ ሚሊዮን ሕዝብ በክልል፣ በአውራጃ፣ በወረዳ፣ በቀበሌ፣ በመንደር እያለ ወርዶ እስከቤተሰብ ድረስ ተጠፍሯል። ኦሮሞው “ኦሕዴድ” በሚባል ቀልቀሎ ተሞጅሯል፣ አማራው ብአዴን በሚሉት ስልቻ ተወጥቋል። ደቡቡም፣ ሲሜንም እንዲሁ በየዘንቢሉ ታሥሮ ተንጠልጥሏል። ዘዴው ከራሺያው ስታሊን የተወረሰ ነበር። ዛሬ፣ ቤተሰቡ ለወያኔ ካላደረ፣ ልጅ ትምሕርት ቤት አይገባለትም። ለወያኔ ያልተገዛ ወጣት ሥራ አይገኝለትም። ዩኒቨርሲት የመግባት ዕድልማ “ኢሕአዴግ” ካልሆኑ አይታሰብም። ለወያኔ የፖሊቲካ ካባ ፓርቲ፣ “ለኢሕዴግ” (እነሱ ሲያቆላምጡት “አድጊ” ይሉታል) ያላደረ ሠራተኛ የሥራ መተማመኛ የለውም። ነገ እንደውዳቂ ዕቃ ተሽቀንጥሮ ይጣላል። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ጉባዔን (ኢሰመጉን) አዳክመው ገድለውታል። የኢትዮጵያ መምሕራን ማኅበርን (ኢመማን) በሕገ አራዊት ወጥሮት በዚያ ስም እንዳይንቀሳቀስ ሲያግድ አባላቱ ሌላ ስም ፈጥረው “የኢትዮጵያ ብሔራዊ መምሕራን ማኅበር” እንኳ ብለው ለመንቀሳቀስ ማመልከቻ ቢያስገቡ፣ “የኢትዮጵያን ስም መጠቀም አትችሉም” ተብለው ተሽመድምደው ተቀምጠዋል። ከውጭ ዕርዳታ እንዳያገኙ “በሕግ” ተከልክሏል። አስተማሪው አፉን ተለጉሞ፣ ተተብትቦ በመቀመጡ ትምሕርቱ እራሱ ታሥሯል። የኢትዮጵያ ነጻ ጋዜጠኞችን ማኅበር ሙሉ በሙሉ በቁጥጥራቸው ሥር አውለውታል። የሠራተኛውን ማኅበርማ ገና ከጠዋቱ ነበር የተቆጣጠሩት። ሁሉ በጃቸው ሁሉ በደጃቸው ሁኖላቸዋል። መሬቱ በጃቸው (እንደፈለጉ፣ ይሸጡታል፣ ይለውጡታል፣ ይለገሱታል)፣ እርሻው በጃቸው፣ ንግዱ በጃቸው፣ ሕክምናው በጃቸው፣ ጦሩ በጃቸው፣ ፍርድ ቤቱ በጃቸው፣ አስመራጩ ድርጅት በጃቸው ... ምን ቀራቸው? በአጠቃላይ አገር ውስጥ ኗሪ ሕዝባችን ሕይወቱ ሙሉ በሙሉ በወያኔ ቁጥጥር ሥር ወድቋል። አንድ ጊዜ አንድ የነደደው ኢትዮጵይዊ ሠራተኛ፣ ወርቃማው አለቃው ጠርቶት የስለላ ሥራ በባልደረቦቹ ላይ እንዲሠራ በግልጽ ሲያዘው፣ ንድድ ብሎት፣ “ይኸንንስ ከማደርግ ለምኜ ባድር ይሻለኛል” ብሎ በድፍረት ተናገረው። ወርቃማው አለቃ እየሳቀ መልሶ፣ “ያንንም እኛ ስንፈቅድልህ ነው” ብሎት አረፈ። ሕዝባችን እስከዚህ ተዋርዷል።
በመዳፉ ሥር ያለው ሕዝባችን አማራጭ በማጣቱ፣ 99.6% ድምጽ እንዲሰጠው ያለምንም ዕፍረት በግድም ሆነ በውድ አስፈጽሞታል። የሚገርመው ባሕር ተሻግሮ ኢትዮጵያዊውን ዝርያ በሙሉ ለመቆጣጠር የነደፈው የረዥም ጊዘ ዕቅዱ ነበር። እኛ ደግሞ ለእንደዚህ ዓይነቱ ዓይን ያወጣ ድፍረት፣ ምቹ ነን። ዕቅዱን አውጥቶ አሠራሩን ነድፎ “የኮንስቲትወንሲ ግንባታ መሪ ዕቅድ” ብሎ ለየኢምባሲው የበተነው በ1998 ዓመተ ምሕረት ነበር። በየኤምባሰው የተኮለኮሉትም ጉዳይ አስፈጻሚዎች ሥራውን በሰፈው ተያይዘውታል። አምባሳደር ካሳሁን አየለ የፈረሙባቸው 21 ደበዳቤዎች ዛሬም አዲስ ቮይስ በሚባል ድረ ገጽ ለሕዝቡ ጥቅም እንዲውሉ ተቀምጠዋል ። ቢንያም ከደር የተባሉ የቀደሞ በኩዌት የኢትዮጵያ እምፓሲ ዋና ጸሐፊ ይኸንኑ በኢትዮሜዲያ ድረ-ገጽ አረጋግጠውልናል።
ውጪ ኗሪ ኢትዮጵያዊ ሳይወድ በግድ ተሰዶ ነው የተበተነው። ያኔ ከቤቱ ከዘመዱ ከአዝማዱ ሲሰደድ አሳዳጁን ያውቀው ነበር። ከሞት የተረፈው ዛሬ ለዚያ የዳረገውን ረስቶት ይሆን? የበረሀውን ሐሩር ተቋቁም፣ የሞተው ሙቶ፣ ባሕሩን ደፍሮ፣ የሰጠመው ሰጥሞ የተረፈው የደረሰበት ደርሷል። አንድ ሰሞን አንዲት ዘመዳችን በሱዳን ሰሐራ በረሀን አቋርጣ፣ በሊቢያ አድርጋ ሜዲቴራኒያን ባሕር በአልባሌ ታንኳ ስትሻገር ብዙ ወገናችን ስምጦ በዓሳ ሲበላ በዓይኗ አይታለች። እሷ በተአምር ተርፋ ማልታ ደረሰች የሚል ዜና ሰማን። ከሎንደን ከቤተሰቤ አንድ ሰው ማልታ ድረስ ሂዶ እንዲጎበኛት ወስንን። አማራው፣ ኦሮሞው፣ ትግሬው ጉራጌው፣ ኤርትራዊው በዘር መከፋፈሉን ወደ ጎን ትቶ “በአብሻ” ስም ተሰብስቦ ተጋግዞ ተጠጋግቶ የማልታ የስደት መተላለፊያ ኑሮውን በመጠለያ ይገፋታል። ታዲያ እነዚህ “አበሾች” ዓሳ አንበላም ብለው እርፍ። ምነው ቢባሉ፣ ዓሳው ወንድምና እህታቸውን ሲባላ ስላዩት እሱን መብላት ወገናቸውን የሆነውን የሰው ሥጋ የበሉትን ያህል ስለሚሰቀጥጣቸው እንደሆነ አስረዱ። በዚህ ሁኔታ ለንዶን፣ አምስተርዳም፣ ኮፐንሀገን፣ ኦስሎ፣ ኢየሩሳሌም፣ ኩዌት ... ኒው ዮርክ፣ ዋሽንግተን፣ ሎስ አንጀለስ፣ ... ኦቶዋ፣ ቶሮንቶ፣ ኦንታሪዮ፣ ... የገባውን ስደተኛ ነው ወያኔ መልሶ ቁጥጥሩ ሥር ለማግባት በሰፊው የተሰማራው። ትንሽም ቢሆን እየተሳካለት ነው። ሆዳም ሞልቷላ። የትላንትና ስቃዩን እንዲረሳ ሆድ አስገድዶት አንዳንድ ወገናችንን ከወያኔ ጋር መወገን ጀምሯል። በጣሊያን ወረራ ጊዜስ ባንዶች አልነበሩ ሕዝባችንን ያስጨረሱት? ዛሬም የባንዳው የልጅ ልጅ ነግሶብን ከወገናችን ደካማ ደካማውን በሆዱ እየገባ እየመለመለ እያበነደደው ነው።
የወያኔን ዘዴ በተለያዩ ጊዜያት አጋልጠናል። ይኸችን ሰሞን እንኳን፣ “እሳት ቢያንቀላፋ ገልባ ጎበኘው” በሚል ርዕስ ወያኔ “የአማራ ልማት ማኅበር ሊያቋቁም” እንደ አውሮፓ አቆጣጠር ሜይ 29 ቀን 2010 ዓ ም (29 May 2010) መጥራቱን በየድረ-ገጹ አጋልጠናል ። በአጭሩ ወያኔ አማራውን ሊያለማ ከቶ ፍላጎትም ሆነ የሞራል ብቃትም እንደሌለው ጸሐይ የሞቀው ሐቅ ነው። ዋናው ቁም-ነገር እና ልፋቱ ሁሉ ስደተኛ አማራውን ተቆጣጥሮት ሊያጠፋው ነው። ወያኔ ኦሮሞውን ሊያለማ ፍላጎት የለውም። ዓላማው ሌላ ነው። ሕዝባችን በዚህ ተታሎ እንዳይሄድ ብንነግረውም፣ የሆድ ነገር ሆድ ይቆርጣል ሆኖበት መሰል 200 የሚድርስ ስደተኛ ሂዶለታል የሚል መረጃ ደርሶናል። ወያኔ ከሌሎቻችን የሚለየው በአንዲት ነገር ነው። የማይቻል መስሎ የሚታየውን ሁሉ ከመሞከር ወደ ኋላ አይላትም።
“የከተማ መሬት ይሰጠሀል” እየተባለ እራሱ ሰው መረማመጃ መሬት እየሆነ የሚነጠፍለት ሆድ አደር እየበዛ መጥቷል። “ግባ ወደ አገርህ። መኖሪያ ቤትህን ሥራ” እየተባለ ተሸውዶ በየወያኔ ኤምባሲው ወዶ እየገባ እጁን የሚሰጥ ሆድ አደርን ያው ከርሳሙ ሆዱ ይቁጠረው። ሲሄድ ታድያ ሙሉ ስሙን፣ አድራሻውን ስጥቶ፣ ስልኩን አስረክቦ ነው የሚመለሰው። በአጭሩ ሒሊናውን ሽጦ ነው የሚመጣው። የወያኔን ወንጀል ለዓለም ሕዝብ ለማጋለጥ ሰላማዊ ሰልፍ በወጣንባቸው ማግስት የወያኔ አምባሳደሮች፣ ያንን በአሥር ሺህ የሚቆጠር ስም ዝርዝር ይዘው በየአገሩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቢሮ መኮልኮል ዓይነተኛ ልማዳቸው አድርገውታል። ምነው ቢባል፤ “እዚህ ሰላማዊ ሰልፍ የሚሰለፉብን፣ በአብዛኛው የደርግ ርዝራዦች ናቸው። በመቶ ሺ የሚቆጠር የኢኮኖሚ ስደተኛ ይኸውና እኛ ጋ ተመዝግቦ ኢሕአዴግ አገር ውስጥ የሚሠራውን የልማት ሥራ በሞራልም በገንዘብም ይድግፍልናል” እያሉ የወያኔ ልዩ መልዕክተኞች ያጭበረብሩበታል። ሒሊና-ቢስነት ይሉሐል ይኸ ነው። ለወገን ደንታ-ብስነት ይሉሀል ይኸ ነው። ለሆድ ሲሉ ወገንን ማስጠቃት፣ ወገንን አሳልፎ መስጥት ማለት ይኸ ነው። ከዚሁ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ዛሬ ሁለት ነገር እንቃኛለን።
፩ኛ - የሎንደኑ የኢትዮጵያውያን የእግር ኳስ ጨዋታ ቡድን
ወጣትነት የእሳት ዘመን ነው። ወጣቱ ስደተኛ የእግር ኳስ ጨዋታ፣ የኢትዮጵያ ዘፈንና ጭፈራ ይወዳል። ወያኔ ሁሉም ቦታ አለ። የወያኔ ባለሥልጣኖች ዓላማቸውን ለማሳካት ሲሉ የአጎት የአክስታቸውን ልጆች በስደተኛ ስም በገፍ ወደ ሎንደን አግዘዋቸዋል። ሥራ ፈጥረውለት መሆኑ ነው። ታዲይ እነዚህ አስመሳዮች ከዕውነተኛ ስደተኞች መሐል በጓደኝነት መልክ፣ በኳሱ ሜዳ፣ በጫቱ በርጫ፣ በየጭፈራው ክበብ ተሰግስግው ሰይጣናዊ የወያኔ ተግባራቸውን በሰፊው ተያይዘውታል። ልብ ማኮላሸቱን ቀጥለውበታል።
እንግዲህ አንዱና ዋነኛው በሎንደን የስፖርት ፍቅር የሳባቸውን ወጣቶች አድብቶ የሚያጠምድ ወያኔ፣ የአቶ አባይ ጸሐይ ቤተሰብ አባል በመሪነት ተሰማርቷል። እያንዳንዱ የዚህ ቡድን አባል ማን ማን እንደሆነ ያውቃል። አላሙዲም ብቅ ሲል ስኳር እንደሚያቅማቸው እናውቃለን። ልጆቹ በተለያዩ ድለላ እንደተያዙም ሳይታለም የተፈታ ሐቅ ነው። ከተለያዩ አገሮች የመጡት ስደተኞች የሚገናኙበት “የዓለም ዋንጫ የእግር ኳስ ጨዋታ ውድድር” በሚል ሰበብ ሰሞኑን በወያኔ ካድሬዎች አነሳሽነት የታቀደ ተግባር ሥራ ላይ በመዋል ላይ ይገኛል። ከየአገሩ ዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ የሚኖሩትን ስደተኞች አስተባብረውም ጨዋታ ጀምረዋል። ታዲያ አንዱ አስገራሚ ነገር፣ የድፍረታቸው ድፍረት ወያኔዎች አንዳንዱን የዋኅ ኢትዮጵያዊ ወጣት አግባብተው፣ እነሱ ያዘጋጁለትን፣ መለያ ልብስ ወይም በተለምዶ ማላያ እንዲልብስ አድርገውታል። ማላያውም የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ የተዋረደባት ጠባሳ አምባሻ መሳይ ኮከብ ምልክት ደረቱ ላይ ደረተውበታል። “ይኸ ቡደን የኔ ቡድን ነው” እያለን ነው ወያኔ! በዚህ የተነሳ ወጣቶቹ እስከመበጣበጥ ደርሰው ግማሾቹ “ይኸንን ሰንደቅ ዓላማችን ብለን ለብሰን አንጫውትም” ብለው እራሳቸውን ሲያግልሉ ሌሎቹ የዋኾች ግን “የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ምንም ኖረበት ምን ያው የኢትዮጵያ ሰንደ ዓላማ ነው፣ ሁሉንም በፖሊቲካ አትተርጉሙት” በማለት ቀጥለውበታል። ባለፈው ሁለት ሳምንት ቻልፎንት ስታዲየም አካባቢ ባደረጉት ግጥሚያ መሸነፍ ደርሶባቸው ተመልሰዋል። ድሮውንም ጎበዝ-ጎበዝ ተጫዋቾች የማይካፈሉብትና፣ ሁለት ልብ ሆነው የሚጫውቱትም ተጫዋቾች ከወገን የሚደርስባቸውን ወቀሳ እያሰላሰሉ መቼ አትኩረው ተጫውተው ውጤት ያገኛሉ? ወያኔ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ያግበሰበሰውና በኢትዮጵያ ስም ለምኖ ያካበተው ገንዝብ አለው። እንደልቡ ሊረጨው ይችላል። ያ ሁሉ ግን የእምቧይ ካብ ነው። ዛሬ ለሆዱ የተሰለፈለት የዋኅ ሕዝብ ነገ ለሕሊናው ይሰለፍበታል። እንዲያ አልነበር በቅንጅት ጊዘ የተፈጸመው? አሁንም ያ ይደገማል።
ሰንደቅአላማችንን በተመለከተ አንጀቴ አርሮ በፈረንጆቹ አቆጣጠር ኖቨምበር 6 ቀን 2000 ዓ.ም በእንግሊዝኛ ቋንቋ የጻፍኩት ግጥም አለ። ከፈለጉ የግል ብሎጌ ውስጥ ገብተው ማንበብ ይችላሉ።
http://wondimumekonnen.blogspot.com/2010/06/scar.html
ሰንደቅ ዓላማችን ተዋርዷል። የተዋረደ ሰንደቅ ዓላማችን ከነአምባሻ ምልክቱ ለብሶ የተጫውተ እያወቀም ይኹን ሳያውቅ፣ ያው እርሱም ወይኗል። የወያኔ ካባ ውስጡ ዳባ ነው። ወያኔ ማላያውን ሲያለብስህ፣ “ተቆጣጥሬህአለሁ፣ የት አባትክ ልትገባ!” እያለህ ነው። አንዱን ሰው አንዴ ማኖ ካስነኩት አለቀለት ብለው ይገምታሉ። የኢትዮጵያው ጠቅላይ ስቃይ አንዴ ለአዲስ ተሿሚ ካድሬዎች ላይ ሲፎክሩ ምን አሉ መሰላቸሁ። “የእሕአዴግ ሥልጣን፣ የዛፍ ላይ እንቅልፍ ነው። ሽልብ ካደረገ ዱብ ነው”። እንደሸረሪቷ ደምን ምጥጥ አድረገው ይተፉታል። ሁለተኛው ጉዳያችን የሚከተለው ነው።
፪ኛ፡ ዲያስፖራው አገር ቤት ገብቶ ንዋዩን እንዲያፈስ ወይም ኢንቭስት (invest) ኢንዲያደርግ የሚደረገው የጠልፋ ሙከራ
አንድ ጓደኛዬ የሚከተለውን ጥሪ “ተመልከት” ብሎ አስተላለፈልኝ።
Dear Ethiopia Investor,
As you know, Precise Consult International has been at the forefront of promoting Diaspora business in Ethiopia. Accordingly, we have been a part of four Ethiopian Diaspora Business Conferences, held in Addis Ababa, Washington DC, and Los Angeles, either as lead organizer or as a major sponsor. This year, on the fifth anniversary of the event, we have once again partnered with the Ethiopian American LLC and USAID Vega Ethiopia to put together what promises to be a historic milestone in Ethiopian business.
*So what’s in store this year?*
For the first time in the history of the event, this year’s conference will be held over two days and will be open to the wider Ethiopian Diaspora public in North America. It will also have a business exhibition from Ethiopia with the aim of helping to establish market linkages between Ethiopian business and the U.S market via the Diaspora. As ever, the topic of doing business in Ethiopia will be thoroughly covered by guests’ speakers already doing business in Ethiopia. This year’s event will also be presided over by a surprise high profile speaker.
*What’s in it for you?*
If you are a business in Ethiopia looking to penetrate the U.S market and would like to participate in the business exhibition, there are still openings left so contact us immediately to arrange the details. If you live in North America and you are looking to connect with Ethiopian businesses or would like to be informed about doing business in Ethiopia, do not miss this historic event. Please feel free to forward this message to all those you know who may be interested in doing business in Ethiopia. The fifth Ethiopian Diaspora Business Conference will be held in Washington, DC, July 11-12, 2010. For more information, please visit www.ethiopiainvestor.com .

ይኸንን ጥሪ ሳነብ ከትከት ብዬ ነበር የሳቅኩት። የሸረሪቷ ነገር እንደገና ታየኛ! ሸረሪት ሆዬ ድሯን አድርታ ካበቃች በኋላ ከአካባቢው ራቅ ብላ ለሆዷ ካንዱ ጥንብ ወደ ሌላው ጥንብ የምትክለፈለፈውን ዝንብ ትጠብቃለች። ሆዷን እንጂ የተደራላትን አሽክላ ያላስተዋለችው ዝንብ በሸረሪቷ ድር ትያዛልች። ሸረሪት ተመልሳ ዝንቧ ገና በሕይወቷ እያለች ድሟን ምጥጥ አድርጋ ከጨረሰች በኋላ፣ ሌላ ራት ለማጥመድ የደረቀችውን ዝንብ ገፍታ ጥላ፣ ድሪዋን ጠጋግና እንደገና ትጠብቃለች። የወያኔም ስልት ይኸው ነው። ገና ከመጀመሪያው እኮ ንግዱንም እንደተቆጣጠረው ከላይ አመልክተናል። ዛሬ በነጻነት የሚነገድ ነጋዴ ወይም የቢዝነስ ሰው የት አለና? በዛሬይቱ ኢትዮጵያ ሁሉም ነገር ሊፈጽም የሚችለው ወያኔ ሲፈቅድለት ቢቻ ነው። እንዳነበብነው ልመናም ቢሆን! ሸክ አላሙዲ የወያኔን ካናቴራ ለብሶ የወጣው በጤናው ነው? ንብረቱን ለመጠበቅ እርሱ ሰውዬው የወያኔ ንብረት መሆን ነበረበት። ነገሩ ግልጽ ነው። “ገንዘብህ ባለበት እዚያ ልብህ አለ።”
ለመሆኑ ይኸ ሚሺን ወይም ተልዕኮ የተሰጣቸው እነማን ናቸው? የሚከተለውን የወያኔ ኤምባሲ ድረ-ገጽ የመልከቱ።
http://www.ethiopianembassy.org/pdf/ADM%20Award.pdf
የሚገርመው ግን የዋሁ ሰደተኛ ማትረፉን እንጂ መዘረፉን ወይም እራሱ መጠቀሚያ መሆኑን አለመገንዘቡ ነው። ንብረት ኢትዮጵያ ውስጥ ማፍሰስ የቻለ ስደተኛ፣ ለምን ውጭ አገር እንደሚኖር በመጀመሪያ ደረጃ አይገባኝም። የአባትህ ቤት ሲዘረፍ አንተም አብረህ ዝረፍ የሚባለውን አባባል ተከትሎ ከወያኔ ጋራ ተባብሮ ሊመዘበራት ከሆነ፣ ያው እሱም ሌባ ነው። ከወያኔ ጋራ ካልተባበሩ ምንም ዓይነት ሥራ ኢትዮጵያ ውስጥ መሥራት አይቻልም። አገሩን የወደደ ኢትዮጵያ ውስጥ ገብቶ የወያኔ እሳት እራት ከሚሆን፣ በመጀመሪያ ደረጃ ቀንደኛውን የኢትዮጵያን ጠቅላይ ሥቃይ ለመገላገል ገንዘቡንም፣ ጉልበቱንም እዚያ ላይ ቢያውል የሕሊናም ዕረፍት ያገኛል፣ ከታሪክም ወቀሳ ይተርፋል።
አንዳንዶቹ ያጋጠሙኝ እበላ ባዮች፣ “ሁሉንም በፖሊቲካ ዓይን አትየው። ጽንፈኛ አትሁን።” ይሉኛል። ፖሊቲከኛም አይደለሁም። ጽንፈኛም አይደለሁም። ዳሩ ግን ወያኔ ላለፉት 19 ዓመታት አገራችንን ሲመዘብራት፣ ሕዝባችንን ቁም ስቅል ስቃዩን ሲያሳየው ዝም ብዬ የምመለከትበት አንጀት የለኝም። ሆድ አደርማ ብሆን፣ ምን ችግር አለ። መኖር እችላለሁ። ወገኔንም ሽጬ ብሆን ተንቀባርሬ መኖር እችላለሁ። እኔነቴን እስካሁን አልሸጥኩትም፣ ወደፊትም አልሸጠውም። እንዲሁ እንደሌሎቹ መሰሎቼ ዕውነቷን ተናግሬ እመሸብኝ አድራለሁ። ለጊዜው እንግሊዝ አገር ተሰደጄ ውዬ ተሰድጄ በማደር ላይ እገኛለሁ።
ወያኔ አሁን አሁን የልብ ልብ ተሰምቶት የሚሠራውን ሁሉ በግልጽ ማድረግ ጀምሯል። የአሜሪካንን ድምጽ ሬድዮ አፍኜአለሁ ብሎ እኮ በግልጽ የተናገረ፣ ትከሻው ያበጠበት ወንጀለኛ ነው። “አገር ቤት ንዋይ አፍስሰን ሕዝባችንን ልንረዳ ነው” እያላችሁ የምትሞዳሞዱት ሆዳሞችም ሆይ፣ አዙሮ ማየት አቅቶአቸው ከወያኔ ጋር የየምትሽኮረመሙ ወገኖቼ፣ ወያኔ ያዘጋጀላችሁን አሽክላ የማሳያችሁ፣ አንዱም ሀቁን ነገሬአችሁ ከምትሄዱበት ገድላማ መንገድ እንደትመለሱ፣ ካልሆነም እኔ ከደማችሁ ንጹሕ መሆኔን ልነግራችሁ ነውና፣ አንዲያው አትናደዱብኝ። የተዘጋጀላችሁን ወጥመድ፣ የሚከተለውን ድረ-ገጽ አንብባችሁ ተረዱ።
http://ethiopolitics.com/news_1/200908241000.html
በዚህ ጥሪ መሠረት እያንዳንዱ ኢትዮጵያ ውስጥ ንዋይ ያፈሰሰ፣ አሻራ መስጠት ይኖርበታል። አሻራ ከሰጠ ቁጥጥር ሥር ዋለ ማለት ነው። እናቱ፣ አባቱ፣ እህቱ፣ ወንድሙ ወይም የቅርብ ዘመዱ እንኳን ቢረሸን በሚኖርበት አገር ሰላማዊ ሰልፍ መውጣት አይችልም። የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሥቃይ መለስ ዘናዊ ለጉብኝት በመጡ ቁጥር እንደ ጭራቅ እንኳን ቢጠላቸው ተሰልፎ እጅ መንሳት ሊኖርበት ነው። ወያኔ ስሙን መዝግባ ይዛለቻ። የሚኖርበትን አድራሻ ታውቃለች፣ ስልኩን ታውቃለች፣ ኢ-ሜሉን ታውቃለች፣ አሻራውን በእጅዋ ጨብጣለች። ያ ማለት ንዋዩን ኢትዮጵያ ውስጥ ያፈሰሰ ስደተኛ ከነዘር ማንዘሩ የወያኔ አገልጋይ ሆኖ እንዲቀመጥ የተደራለት ድር መሆኑን ይገንዘበው። አንዴ ወያኔ ከነጀሰህ በኋላ፣ ከሕዝቡ ካላተመህ በኋላ፣ ውኒጥ-ውኒጥ ማለት ትርፉ ለመላላጥ ብቻ ነው። በመጀመሪያ አትለከፍ። አንዴ ከተለክፍክ፣ ዘልዓለም ጠባሳው ይከተልሀል። ታርጋው ተለጥፎልህ፣ ከተገላገልከውም በኋላ “የወያኔ አሽከር” እንደተባልክ ትኖራለህ። ወገኔ ከዚህ መዓት እራስህን አድን። አይድረስባችሁ!
ባለፈው ግንቦት አንድ የወያኔ አሽከር እዚህ ሎንደን ውስጥ ሊበራል ዲሞክራትን ወክሎ ለፓርላማ ተወዳደረ። ይኸ ሰው በሄድንበት እየተከታተለን፣ የወያኔን ወንጀል በአጋለጥን ቁጥር ሽንጡን ገትሮ፣ አይኑን በጨው አጥቦ፣ ወሸት አንግቦ የሚከራከረን ሰው ነበር። ታዲያ ይኸ አጭበርባሪ በዚህ ዲሞክራሲ በሰፈነበት አገር፣ በሱው ብሶ እንግሊዝ ፓርላማ ገብቶ ለወያኔ ወኪል ሆኖ ሊያገለግል ሲጥር ደርሰንበት “አይሆንም” ብለን ተቃወምን። ታዲያ አንዳንድ የዋሆች፣ “ምን አለበት። እናንተ ማድረግ ያቃታችሁን ትልቅ ነገር እሱ ዕድሉን ቢሞክር። እናንተ ምቀኝነት ይዞአችሁ ካልሆነ ወገናችሁን እንዴት ትቃወሙታላችሁ” ብለው ሊጋፈጡን ሞከሩ። ወገናችን? እንዲህም አድርጎ ወገን አላየነም! ከዚህ በፊት ወያኔን ደግፎ ሲነታረከን የተነሳውን ፎቶራፍ እያሳየናቸው ለማሳመን ሞክረን። እርግጥ ብዙ ሰው አሳምንናል። ስንቱ ግን ያልነቃ አለ! ሰንቱ ገና ይነጫል። ስንቱ ገና ይሞሸለቃል! ስንቱ ገና ይበላል! ስንቱ ገና ይታለላል! አሁንም የሚገርመኝ፣ ይኸንን ሁሉ የማጋለጥ ሥራ እየሠራን፣ “ወያኔ ሊሞጨልፋችሁ ነው ተጥንቀቁ” እያልን ተታልሎ፣ ተታልሎ የወያኔ እሳት እራስት እየሆነ ያማያልቅ ሕዝብ እንደ አሸን መፍላቱ ነው። ተስፋ የማትቆርጠዋ የወያኔ ሸረሪት ሳትቦዝን ነጋ ጠባ ድሯን አድርታ ትጠብቀናለች። ልንበላ ገበተን እንበላ ጎብዝ! ተደግሞብናል ልበል? ጋግርቱ ይለቀን እንደሆን እሲቲ ወደ ፈጣሪ ኢግዚዖ እንበል! ኢግዞዖ!

Wednesday 9 June 2010

THE SCAR!

A star?
What star?
I don't see any star!
But I do see something else!
A torn flesh, deep scar!
A wound cut to divide,
Curved out on our flag;
Inflicted on our pride,
Engraved traitors tag.
A star?
Why a star?
For a star we do care less,
It's nothing to do with us;
Irrelevant meaningless,
An alien from the distance!

A star?
What star?
That is not the Star of David,
May be of snakes and lizards;
Tarot reading magic wand,
Ashtaroth of witches and wizards.
Rise up Ethiopians!
No time to decide!
Resurrect your defiance!
You're condemned to genocide!
Our insignia is desecrated,
Bearing a scar on the chest,
Marked to be sacrificed,
Like the Jews at Holocaust,
When a nation is humiliated,
The flag suffers first.

Hyenas are inflicting pain,
Though wolves fell of the race;
The lion is removed again,
Ashtaroth took his place;
Under the yoke of these thugs
We remain deeply hurt
The star remains on our flag
The scar remains in our hearts

Don't touch the scarred flag,
That is not the real one;
It is the one turning rag,
Ours is smooth and plain.
Green as a fertile land;
Yellow faith of pure gold
Red hot patriot's blood;
Pride of every household.

Don't give up compatriots!
Victory is yet to come;
We shall march as patriots;
Joined united as one!


Our flag has the power;
The lion is her emblem;
Hoisted on the highest tower;
Heralding long freedom!
The Lion!
The sign of resistance,
Defeated but not conquered
The Symbol of defiance,
Tired but not surrendered.
Keep our flag neatly;
Enemies would love to burn,
Ethiopia waits patiently,
Her roaring lion's return.






WAKE UP MY PEOPLE!!!!

Wondimu Mekonnen
London
06/11/00

Saturday 29 May 2010

እሳት ቢያንቀላፋ ገለባ ጎበኘው

ወንድሙ መኰንን

የኢትዮጵያው ጠቅላይ ስቃይ መለስ ዜናዊ ከምንጊዜውም በበለጠ የማጭበርበር አክሮባት ሠርተው የኛው አባ ጉልቤ “በእንከን የለሹ” ብሔራዊ ምርጫ “ተቃዋሚውን አፈር ድሜ አስግጬው አሸንፍኩ” ብለውን አቅራሩብን! ዓለም አቀፍ ታዛቢዎችም ከዚህ በፊት አይተው የማያውቁት ትርዒት በዝምታ እንዲመለከቱ ተገደዱ። አሜሪካኖቹ ሳይቀሩ በየኤምባሲአቸው እንዲቀረቀሩ ታዘዙ። እንዲህም አርጎ ምርጫ የለም። አባ ጉልቤ ማንን ከመጤፍ ቆጥረው! በአሁኑ ጊዜ እንኳን ለሌላው እና ለታማኙ ተቃዋሚአቸው ለአቶ ልደቱም አልራሩ። ሁሉንም ጠቀለሉት ጃል! አቶ ልደቱ ትንሽ ተዳፈሩ መሰለኝ። በቴሌቪዥን ክርክሩ ጊዜ ምን ያህል መንጠራራት እንደነበረባቸው አቅማቸውን ባለመገምታቸው ገደብ አለፍ አሉ መሰል። ሊቀ መኳሳቸው ፕሮፌሰር ኤፍሬም ይሰሐቅ መክረኛውን ኃይሌ ገብረሥላሴን ይዘው አንድ ነገር እንዲፈጽሙ ተነግሮአቸዋል። ምን ይታወቃል፣ አቶ ልደቱ አቅማቸውን ካወቁ በኋላ፣ በድርድር ሚኒስቴር ሊሆኑ ይችላሉ። ኢሕአዴግ እንደ እግዚአብሔር መሐሪ ሆኖ የለ? በሌላ በኵል ደግሞ፣ በረከት ስምኦን ጋር ፎቶአቸውን እንደባንዲራ እያውለበለቡ፣ ከአብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር ያላተሙአቸውንም እንጂኒየሩም ሳይቀሩ በዘሮ ዘረሩአቸው። አሁን እንጂነየሩ እንደተቀየሙ እንዳይቀሩ፣ ምናልባት ፕሮፌሰር ኤፍሬም አሁንም ተዓምር ሊሠሩ ይችላሉ። ክፍት የአማካሪ ቦታ አለ የሚል ፍንጭ እየሰጡን ነው። እርስ በርስ ያናኮሩትም አንድነት ምንም አልበጀው። ብርቱካን እስር ቤት እንደተዘጋች እንዳትሞት እና የሕዝቡን ቁጣ እንዳታነሳ፣ ምናልባት አሁንም ኤፍርም የሚሠሩት ተአምር ሊኖር ይችላል። አቶ መለስ፣ ዋናውን ተፎካካሪአቸው አቶ ስዬ አብራሀን በዚህኛውም መስክ ያለርህራሔ በባዶ ረቱአቸው፡፡ የሕዝቡን እጅ በግድ ጠምዝዘው 99.4% (0.6ቷ የተገባች) ድምጽ ለወያኔ አስመዝግበዋል። የኢሰፓ/ደርግ ፖሊቲካ ጊዜዋን ጠብቃ በሾርኒ ብቅ አለች አይደል? በወያኔ የብሔራዊ ክደት ባለሟሎች ጥቅም ላይ ዋለች እንደገና? ደርጎች ነብሳችሁ አይማርም። አንድ ተጨማሪ ተንኰል አስተምራችሁ ሄዳችሁ። ሰሎሞን ተካልኝ የተባለ ገንዘብ እየተከፈለው የሚዘፍን የአገራችን የጠጅ ቤት አዝማሪ ቢጤ እበላ ባይ ሰው፣ ስንት ብር ግንባሩ ላይ እንደለጠፉለት አይታወቅም፣ ጋንጩሩን አስቀየሚ መለስ ዜናዊ፣ “ቅንድቡ ያማረለት ቆንጆ፣ ምሑር የምሑራን ቁንጮ” እያለ እንዲዘፍንላቸው ግጥም አቀበሉት። ይኸም አልበቃ ብሎአቸው፣ መስቀል አደባባይ በስሜት ገንፍለው ወጥተው ፈንጭተዋል። ግን የፈነጩት ጥይት ከማይበሳው መስታወት በስተጀርባ ነው። ፈሪ ጨካኝ ነው።
የወያኔ ባለሥልጣናት፣ የአገር ቤቱን ሕዝብ አንዴ በክንዳቸው ካዳሸቁት በኋላ፣ ዓይናቸውን በጨው ሙልጭ አድርገው አጥበው፣ ምንም ሳያፍሩ (ድሮስ ማፈር መች ተፈጥሮባቸው?) ውጭ አገር ተበትኖ ወደሚኖረው ስደተኛ ኢትዮጵያዊ በአንድ ልብ ፊታቸውን አዙረዋል። ቢሳካም ባይሳካም ሁሉንም መሞክራቸው መቸም አይቀርም። አዳሜ፣ እየመጡብህ ነውና ስደተኛ ሁሉ ጥግ ያዝ! ወያኔዎች ያንን የቀልድና የልጆች የዕቅ-ቃ ጨዋታ መሰል ምርጫ ላይ ድል ሲቀናጁ፣ ውጭ አገር የተነሰነሱት አሽክሮቻቸውም ጌቶቻቸውን ለማስደሰት አልተኙም። አማራውን በአሞሌ ጨው እያባባሉ በጠነዛው ጉሮኖአቸው ሊሞጅሩት ሰሞኑን አንድ ዘግጀት ለንዶን ውስጥ ደግሰዋል። ሆዳሞቹ ከርሳቸውን ለመሙላት ይሄዳሉ። ሆድን የሚያክል ክፉ አውሬ! ወጥመዱ ውስጥ የሚገቡላቸው አይታጡም። ኢትዮጵያውያን ግን ለሌላ ዙር ትግል እየተደራጁ ነው።
ከዚህ በፊት “ጥጃ ለጅብ?” በሚል አርዕስት አንድ መልዕክት ሞጫጭሬ ነበር። ካላዩት፣ የሚከተለውን የግሌን ድረ-ገጽ ወይም ብሎግ ይመልከቱ። http://wondimumekonnen.blogspot.com/
በዚያ ርዕስ እንድጽፍ ያኔ ያስገደደኝ ምክንያት በዚያን ሰሞን ወያኔ እንደዛሬው ወጥምድ ጠምዶ ስደተኛውን ሊመዝብር ደርሰንበት ነበር። በጊዜው የለንዶኖች የወያኔ ጥቅም አስጠባቂዎች በኤምባሲው አማካኝነት በአካባቢው ኗሪ ስደተኛውን ኢትዮጵያዊ ሕብረተሰብ በየሬስቶራንቱና በየመጠጥ ቤቱ እያደኑ፣ “አገራችሁ በጣም ተሻሽላለችና፣ ገንዘባችሁን በፓውንድ ኢትዮጵያ ባንኮች ውስጥ አስቀምጡ። ወለድ ይወልድላችሁአል። በፈለጋችሁ ጊዜም ልታወጡት ትችላላችሁ፤” እያሉ በተለመደው የቁጭ-በሉ ታክቲካቸው ሊያታልሉ ስሞክሩ ነበር “ጅብን ጥጃ ጠብቅ ብለው አምነው አይተውለትም” ብዬ ወገኔን ያስጠነቀቅኩበት። ወያኔ የውጭ ምንዛሪ ባገኘው መንገድ ለመመዝበር አስቦ አልሰሜን አባብሎ አስግበቶ ለመሞጭለፍ የነደፈው ታክቲክ ውሀ በላው። አይታሰብም! ወገናችን ነቃ። ዕቅዳቸው ከሸፈ። ጎበዝ!! አሁን ደግሞ ሌላ የባሰ ተንኰል እየመጣብህ ነውና፣ ኢትዮጵያዊ ሁሉ እጂጌህን ሰብስብ። በያለህበት ንቃ! ለወያኔ አትታለል። ለነዚህ የቀን ጅቦች እራስህን አትሰዋ። ኦሮሞን፣ አማራን፣ ወላይታን፣ ሲዳማን፣ ጉራጌን እየነጠሉ፣ በልማት ማኅበር ስም እየከፋፈሉ ዲያስፖራውን ሊያዳክሙ በአጭሩ ታጥቀው ተነስተዋልና ተዘጋጅተን እንጠብቅ። ከዚህ በፊት በፍረንጆቹ አቆጣጠር 2006 ዓመተ ምሕረት ላይ፣ በያለንበት ሊያኮላሹን የነደፉቱትን 52 ገጽ የፈጀ እቅዳቸውን አግኝተን ይፋ አድረግን ነበር። ካላዩት፤ የሚከተለውን ድረ-ግጽ በአስሊ መኪናዎ አመልካች ጠቁመው ያንብቡ።
http://www.ethiomedia.com/carepress/attack_on_diaspora.html
የወያኔ አሽከሮች፣ ያንን ሰነድ ሥራ ላይ ለማዋል ዛሬም ሌት ተቅን ይባዝናሉ። እንቅልፍም አይተኙም። ተኝተውም አያድሩም። ነገር ሲጎነጉኑ ውለው ነገር ሲጎነንጉኑ ያድራሉ። ሰሞኑን በጉያቸው ሸጉጠው ብቅ ብቅ ያሉባት ታክቲክ በጎን ሲታይ አያ ጅቦ ሆዬ ጥጃውን እራሱን “ና! ለምለም ሳር ያለበትን አውቃለሁ። ንጹህ ውሀ የሚፈስበትን ምንጭ አሳይሀለሁ፣ ደግ እረኛህ እኔ ነኝ። ና ላሰማራህ!” የሚል አባባይ ደም የጠማው ተንኰለኛ ተኵላ ይመስላል። ይኸ የወያኔዎቹ እንቅስቃሴ፣ ከወጥመድነቱም ባሻገር፣ አማራው ላይ የወረደ ስድብ ነው። ወያኔ አማራን ሊያደራጅ! ጉድ ነው!
ወያኔ ትላንትና “አማራ ጠላታችን ነው። አማራ ጨቋኝ ነው። አምራ ነፍጠኛ ነው” እንዳላለ፣ አሁን ደግሞ “አማራውን በልማት ማኅበር ላደራጅ” ብሎ “ተቆጣጢርና ደምሲስናውን” ስትራተጂ ነድፎላችሁ በአጭሩ ታጥቆ በድፍረት ተነስቷል። ጅል አማራ-አማራው እየተመረጠ ይጃጃልለት እንዶሆነ እንጂ፣ መቸም በጤናው ስድቡን እየጠጣ ከወያኔ በታኝ ቡድን ጋ በደኅና አዕምሮው የሚተባበር ይኖራል ብዬ አልገምትም። ይኸ አባባሌ ታዲያ ሆድሞችን አይጨምርም። ሒሊና ቢሶችን ቁጥር ውስጥ አይገቡም። ሆዳሞቹማ አይደሉም እስከዛሬ ያስጠቁን? ወያኔዎች እንዲህ የሚል ድብዳቤ ለጥቁር (ተለጣፊ) አማሮች፣ ለአስመሳዮችና እንዲሁ ለየዋሆች ልከዋል!።
“አልማ (አማራ ልማት ማኅበር መሆኑ ነው) 2002 ... በቅርቡ አዲስ አበባ ሚሌኒየም አዳራሽ በተካኼደ የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት 1.2 ሚሊዮን ብር ገቢ ማሰባሰብ ችሏል።
በዚህም መሰረት በእንግሊዝ አገር አልማ ኮሚቴ ተቋቁሞ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ሲሆን፣ እ.ኤ.አ ሜይ 29 ቀን 2010 አቶ ሕላዊ ዮሴፍ የአማራ ልማት ማኅበር (አልማ) የቦርድ ሊ/መንበር በተገኙበት ታላቅ የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጀት ይደረጋል።
ስለሆነም በዚህ ታላቅ ዝግጀት ላይ ተገኝተው የበኩልዎን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጥሪአችንን እናቀርባለን።”
“አልማ” አሉት? “አጥፋ” ባሉት ባማረላቸው። “የአማራ ጥፋት ማኅበር”!!! ገሩምና ደግም ልክ ነው። የግብዣ ደብዳቤው ላይ የኢትዮጵያን ኤምባሲ ማኅተም ጉብ ብሎበታል። አምባሳደር ብርሀኑ ጥሩ ግልጋሎት እየሰጡ መሆን አለበት። ቦታውም እዚያው “ኢትዮጵያ ኤምባሲ ነው”። ጃንሆይን ያመስግኑ። ምን የመሰለ የተንጣለለ ቤት ለነዚህ ጉዶች ጥለውላቸው አለፉ። ወያኔዎች አንዴ ቤቱን ሊሸጡት ሲያስማሙ ነበር። ንጉሡ አንድ ያሠሩት ሕግ ነገሩን አፈረሰባቸው መስል መሸጥ አቃታቸው። ጉድ ነው። እንግዲህ በዚሁ አዳራሽ ነው የአማራ ጥፋት ማኅበር ሊደራጅ የተደገሰለት። ወያኔ አማራን ሊያደራጅ!!! ያውም በልማት ማኅበር አደራጅቶ እንደከብት ሊነዳ! እኔ ልንገራችሁ ቁርጡን! ወያኔ ያደራጀው አማራ፣ ዝናብ ያጨቀየው አቧራ!!! የጨቀየ ጭቃ ልብስና ጫማ ከማቆሸሽ ባሻገር ለምን ይጠቅማል? ጭቃን እያነሱ የሆን ነገር ላይ፣ ከመልደፍ፣ ከመደፍደፍ፣ ከመለጠፍ፣ ከመመረግ በስተቀር ምን ይደርግበታል? ከወያኔ የሚተባበር፣ ያው ተለጣፊ ጭቃ አይደል? የጭቃም ጭቃ! አንድ የምወዳቸው አዛውንት አንዴ የሆነ ነገር ግርም ብሎአቸው በአንድ ስብሰባ ላይ፡ “የቸገረው ዱቄት ከነፋስ ይጠጋል” ብለው አስደመሙን። ዱቄቱስ መጠጊያ አጥቶ ነው ከበታኙ የሚጠጋው፣ ስደተኛው አማራ ምን ቸግሮት ነው ከአራጁ ጋር የሚውለው? የወያኔስ ድፍረት አላበገናችሁም? “እሳት ቢያንቀላፋ ገለባ ጎበኘው” ይሉሀል ይኸ ነው። አማራው ያለወትሮው ተኝቶ ሲገዛላቸው የወያኔዎች ድፍረት ድንበሩን ጣሰ። ማፈር ቀረ። መፍራት ቀረ። ጎበዝ አንድ በሉ!!
እስቲ ከድሮው የወያኔ ካድሬ፣ አሁን እራሱን ነጻ ካወጣው፣ ከተስፋዬ ገብረአብ መጽሐፍ ትንሽ እንመልከት። (ነገሩን ያገኘሁት ከ”ደራሲው ማስታወሻ” ተስፋዬና አንዳርጋቸው ካደረጉት ውይይት፣ በ125 ገጽ ላይ ነው)።
“በኢህአዴግ የድርጅት ኮሚቴ ደረጃ ውይይት ከተደረገበት በኋላም፣ ኢሕዴንን ወደ አማራ ድርጅትነት ለመለውጥ ጥናት ይደረግ ተባለ። ጥናቱ “አማራነት ምንድነው?’ ለሚለው ጥያቄ ምላሽ እንዲሰጥ መመሪያ ተሰጠ። ክዚህ በሁዋላ ቀጣዩ ጥያቄ፣ ጥናቱን ማን ይስራው?’ የሚል ነበር።

አንዳርጋቸው ትረካውን አቋርጦ መሳቅ ጀመረ።

ምንድነው የሚያስቅህ?’ አልኩ

‘ጥርናቱን ማን እንዲያካሄድ እንደተወሰነ ታውቃለሁ?’

‘ማን ሆነ?’

‘በረከት ስምኦን”

በረከት እኮ ማለት አማራን በጣም የሚጠላ፣ አማርኛን መናገር የሚጸየፍ፣ የዞረበት ዘረኛ ዜጋ ነው። ለምሳሌ በቪኦኤ ትግርኛው ፕሮግራም ቃለ መጠይቅ በደስታ በትግርኛ ሲሰጥ፣ እንግሊዝኛው ፕሮግራም ላይ ቀርቦ በእንግሊዝኛ ሲንተባተብ፣ በአማርኛው መርሀ ግብር ላይ ግን አማርኛ ላለመናገር ጨርሶ የማይካፈል፣ ጸረ አማራ ስሜት የተጠናወተው ጠብራራ ፍጡር ነው” ሲፈጠር ክፋትና ውሸት አብሮት ተፈጥሮ አብሮት ያደገ ያጨካኖች ቁንጮ ሲሆን፣ ወያኔ በመልኩ የጠፈጠፈው የአማራው፣ ድርጅት መሪ ነው። ምን እሱ ብቻ፣ ተፈራ ዋልዋ የተባለ ዘረኛ፣ አንዲት ጠብታ የአማራ ዘር በማይስክሮስኮ ሥር ቢመረመር የማይገኝበት ፣ (ተስፋዬ ገብረአብና አንዳርጋቸው የጊሚራ ተወላጅ ተወላጅ ነው ይሉታል መጽሐፉ ውስጥ)፣ የአማራውን ድርጅትን ቀፍድዶ ይዞ አመራር ላይ ጉብ ብሎ የወያኔን ጉዳይ ያስፈጽማል። እነዚህ ሁልቱ መርዘኞች ነበሩ፣ ዲላና አዋሳ በተካሄደው ስብሰባ “የኢህአዴግም፣ የደቡብ ሕዝብም ጠላቶች አማራና ጉራጌ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ናቸው” ብለው መርዝ ሊረጩ ሲሞክሩ፣ የወላይታና የሲዳማ ብሔረሰብ አባሎች አዋርደዋቸው የመለሱአቸው። ተፈራ ሲናገር፣ “የአማራ ብሔረስብ አይታመንም። ዝም ብሎ አድፍጦ ጠብቆን በካርዱ አደባየን” ብሎ ስሞታ አሰማ። እስቲ ይታያችሁ፣ እነዚህ አማራ ላይ በቂም በቀል የተመረዙ ነበሩ እንግዲህ የተለጣፊው አማራ ብሔረሰብ ድርጅት መሪዎች የሆኑት። ተወልደና አለምሰገድስ ቢሆኑ ትግሬ ሆነው ሳሉ፣ የአማራው ድርጅት ፈላጭና ቆራጭ ሆነው መሰየማቸው ምን ይባላል?

አንዳርጋቸው ንግግሩን ቀጥሎ ተስፋዬን እንዲህ ይላል መጽሐፉ ውስጥ።
“የአማራ ማንነት በረከት ስምኦን እንዲያጠና ታዘዘ። አያይዞ በረከት ቀጠለ። በረከት ስምኦን ጥናቱን ኣጥንቶ ጨርሶ ይዞ መጣ። የሚደንቅ ጥናት ነበር። ፅሑፉ ገና ሲጀምር አማራውን ያወግዛል። አማራው ሌሎች ብሄርብ-ሄረሶቦችን እንዴት እንደጨቆነ ይተነትናል። የአማራው ነፍጠኛ ሌሎች ላይ አደረሰ የሚለውን በደልም ያብራራል። አማራው ሌሎች ሕዝቦች ላይ ፈጸመ የሚባለውን ግፍ አንድ በአንድ ለቅሞ ጽፎአል። በረከት ይሔን ሁሉ አንብቦ ሲያበቃ፣ ‘አማራነት ምንድነው ለሚለው ጥያቄ ምላሽ እንደሰጠ ተማምኖ ወረቀቱን አጣጠፈ።”
እንግዲህ እንዲህ ዓይነት ዓይኑን ያፈጠጠ፣ ጥርሱን ያገጠጠ ጥላቻ የተፈጸመው አገር ቤት ባሉት አማሮች ላይ ነበር። ያም የሆነው አማራ ነን የሚሉ እንደጉልቻ የተጎለቱ፣ እንደ ጉቶ ግማጅ የተተከሉ ባሉበት መድረክ ነበር። በጠመንጃ አፈሙዝ አስገድደው ኣማራው ስድቡን ጠጥቶ፣ ውርደቱኝ ችሎ አገር ቤት አፍዝ አድንግዝ የደገሙበት ይመስላል። ግን ለንዶን ድረስ በድፍረት መጥተው የአማራ ልማት ድርጅት እናቋቁማለን ብለው ሲወዛወዙ ማየት፣ “እውነትም አማራ ተቀልዶበታል” ያሰኛል።
አማራ ነን እያሉ፣ አማራውን ለመቅበር ጎድጓድ የሚቆፍሩ የወያኔ ቅጥረኛ ኩሊዎች፣ ኦሮሞ ነን እያሉ ለሚበደለው ኦሮሞ መቃብር የሚምሱ ሆዳሞች ሞልተዋል። እዚህም ቤት እዚያም ቤት ሞልተው ተርፈዋል። የወያኔ ዓላማ እነዚህን ሆዳሞችን ተጠቅሞ በዘር ከፋፍሎን ኢትዮጵያን ብትንትኗን ሊያወጣት ነው። የዚህ ወይም የዚያ ብሔር ልማት እያለ ገንዘብ ይሰበስባል። ዳሩ ግን የአማራውም ሆነ የኦሮሞው ሕይወት ግን ከድጡ ወደ ማጡ ሲዘቅጥ እንጂ ሲሻሻል አልታየም። ለሆዳሞቹ፣ አንድ መልዕክት አለኝ። መልዕክቱም ሲወርድ ሲዋረድ ከአባቶቻችን የመጣ ነው። በሱው ልዝጋው ጦማሬን።
እዚያም ሂዴሽ በላሽ፣ እዚህም መጥተሽ በላሽ
ሰው ታዘበሽ እንጂ፣ ሆድሽን አልሞላሽ!

Thursday 27 May 2010

ሆ ሆ ይ! ጥጃ ለጅብ?

ወንድሙ መኰንን

“አይሰማ ጆሮ፣ አይውጥ ጉሮሮ” ይሉታል አበው ሲተርቱ። ሌላው የምወደው አባባአል “ጆሮ ምነው አታድግም?” ቢሉት “ይኸን ሁሉ ጉድ እየሰማሁ እንዴት ልደግ?” ብሎ ያለው ነው። አንዳንዴ አንድን አስዳናቂ ነገር በቀጥተኛ አማርኛ ቢሉት አንጀት ስለማያርስ ዘይቤዎች በበለጠ ያብራሩታል። የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሥቃይ መለስ፣ ዜናዊ ሕዝቡ በነገር እየጎነተላቸው ሲያስቸግሩአቸው አንዴ ንድድ ብሎአቸው “እኔስ የሰለቸኝ፣ የአማርኛ ተረትና የአፋር ባጄት ነው።” ሲሉ ተደምጠዋል። የአማርኛ ተረትና ምሳሌ እርቃናቸውን ያስቀራቸዋላ!
ወያኔ በመባል የሚታወቀው የዘራፊ ቡድን በሚያስደንቅ አኳኋን የስልጣን ልጓም ከጨበጠ ወዲህ ብዙ ብሔራዊ ጥቅሞችን አሳልፎ እንደሸጠ ጸሐይ የሞቀው ሀቅ ነው፡፡ ገንዘብ ካየ ይኸ የወንበዴዎቹ መንጋ የእናትንም ሬሳ ከመሸጥ የማይመለስ የሼክስፒሩ ሻይሎክ ነው። በረሀ እያለ ያካሄድ የነበረውን ተራ ውንብድና አቶ ገብረመድኅን አርአያ ቁልጭ አድርገው አንድም ሳያስቀሩ እንደመስታወት አሳይተውናል። ኢግላን፣ አሊጤና፣ ባድሜን፣ ጾሮናን፣ ዛላ አንበሳንና መላውን የኢሮብን መሬት እንዳለ ለሌብነት አስተማሪው፣ ለሻዕቢያ በዱቤ እንደቸበቸበው በታላቁ ሴራ መጽሐፋቸው አስተምረውናል። ነገሩ፣ “ማን ይናገር የነበረ፣ ማን ያርዳ የቀበረ” ነዋ! የትግራይ ሕዝብ መሬቴን አላስረክብም ብሎ ባነሳው ግርግር፣ ሌላው ኢትዮጵያዊ ወንድሙ ደርሶለት የደም ዋጋ ከፍሎ ውሉን አፈር ድሜ ቢያስግጠውም፣ መዘዙ እስከዛሬ ድርስ ተምዞ አላልቅ ብሎአል። ኢትዮጵያውያን በደማቸው የተቤዡትን መሬት መለስ ዜናዊ በቅልጥፍናቸው አልጄርስ ድረስ ሂድው አስረክበው መጡ። አባ ግድየልሽን ማን ጠይቆአቸው? የትግራይ ሕዝብ ግን ወይ ፍንክች! ወደፊት ከአቶ ገብረመድኅን አርአያ ጋር አንዳንድ ጉዶችን በሰፊው ልንዳስስ በዕቅድ አሳድረነዋል። ዛሬም ይኸ የወንበዴ ቡድን በተአምር መንግሥት ሆኖም ያንኑ የበረሀ ውንብድብናውን በሰፊው ቀጥሎበታል። ሊትወው ክቶ አልሆነለትም። ሌባ ላመሉ ዳቦ ይልስ የለ! ሲልከሰከስ የተጠናውተው ሰይጣን መቸ በቀላሉ ይለቀውና! ጠብልም እዚህ ላይ ዱልዱም ነው። ዛሬ ወያኔ አገሪቷን ያለ ባሕር በር አስቀርቷታል፡፡ ወልቃይት ጠገዴን ከጎንደር አውጥቶ ወደ ትግራይ ከቶታል። ነገሩ ካንዱ ክፍለ ሀገር መሬት ቆሮሶ ወደሌላው ማሸጋሸግ ይኸን ያህል ባላስመረረን ነበር። ትግራይም የኛ ናት። አገራችን ናት። ግን ትግራይን እንደገንዘቡ ስለሚቆጥራት (ትግሬዎች ኡ! ኡ በሉ! ተዋርዳችኋምል!) ነገ ትርፍ ካገኘ ከመቸበችባት ወደ ኋላ እንደማይል ስለተረዳን ጥሩ ዋጋ እንድታወጣለት አቅዶ ኢያሰባትና እያደለባት መሆኑ ታይቶን ነው እንልፍ የሚነሳን። ጠርጥር! “አለማታለሁ” አለ? “አደልባታለሁ” ቢለን ግልጽ ይሆን ነበር። ከዚያም አልፎ የአጼ ቴዎድሮስን የትውልድ ስፍራ፣ ሁመራንና መተማን ለሱዳን ሽጦታል። በአገሪቱ ያሉትን ለም መሬቶች ለሳውዲ አረቢያ እየቸበቸበ ነው። ትንሺቱ ጅቡቲ ሳትቀር ከዚሁ ወንበዴ አማካይነት ከኢትዮጵያ ከምትገፈው የወደብ ክፍያ መልሳ የኢትዮጵያ መሬት በርካሽ እየገዛች ባለርስት ሁናለች። “ትንሽ ቆሎ ይዘህ ከአሻሮ ተጠጋ” ይሉሀል ይኸ ነው። ሱልጣን ኢብራሂም እብን አህመድ ትንጥዬ ቦታ አሰብ ሰላጤ ውስጥ ለመርከብ ማረፊያ ለሩባቲኖ ኩባንያ (Rubattino company) ሽጦ አልነበር ጣሊያን ኤርትራ የምትባል ቅኝ አገር ለመፍጠር በቅታ ዛሬ ወደብ አልባ ያረገችን? ጂቡቲ ታሪክ ላትደግም ምን ያግዳታል፣ ከሀዲዎች ኢትዮጵያን እስካስተዳድሩአት ድረስ? ዕድሜ ለወያኔ፣ አሁንም የወደብ ጥገኛዋ ሁነናል። አንድ ሰሞን መርካቶ ለአንድ የሩቅ ምሥራቅ ቱጃር ሊቸበቸብ ነበር ሲባል ሰምተን ነበር። ውሉ የት ደረሰ? መርካቶ እስከዛሬ ካልተሸጠች፣ አይቀርላትም። አንድ ቀን ጆሮ ግንዷን ብሏት ኢትዮጵያዊነቷ ተሰርዞ እርፍ ትላታለች።
ወያኔ ገንዘብ ከሸተተው ይሉኝታ አያውቅም። ድሮውንስ ቢሆን ኢትዮጵያዊ ይሉኝታ መቸ ተፈጠረበትና? እንኳ ኢትዮጵያዊ ይሉኝታና ሽታውም ባጠገቡ ዝር ብሎበት አያውቅም። አባሎቹ ሲሰርቁ ቢያዙ “ምን አባክ አገባህ/አገባሽ?” ብለው መልሰው የሚያፈጡ ዓይን አውጣዎች ናቸው። “የሌባ ዓይነ-ደረቅ መልሶ ልብ ያደርቅ” ይሉታል ይኸ አይደል? ወያኔን በአስታውስኩ ቁጥር አንድ የዛሬ 22 ዓመት ገደማ ያጋጠመኝ ሌባ ትዝ ይለኛል። ከጓደኛዬ ጋር ከፕያሳ ስድስት ኪሎ ለመሄድ ታክሲ ልንሳፈር በሩን ስከፍት አንድ ሰው ተንደርድሮ መጥቶ ገፍቶሮኝ ሾፌሩን “ማርካቶ” ይለዋል። መገፋቴ ሲደንቀኝ እጁ የውስጥ ደረቴ ኪስ ገብቶ ሲበረብረኝ አገኘሁት። በደመ-ነፍስ ያዝኩት። በሰውነት ከኔ የማይሽል ነበረና እጁን ከኪሴ ፈልቅቄ አውጥቼው ሳላውቀው በኃይል ጠመዘዝኩት። አቶ ሌቦ ሆዬ በሱው ብሶበርት በጣም ተቆጣኝ። ኩስትር ብሎ ዓይን ዓይኔን እያየ “በቃ ነቅተሀል! ምን ሙዝዝ ትልብኛለህ። ልቀቀኝ! የማነው ሞዛዛ! ፋራ!” ብሎ እንድብራቅ ሲጮኽብኝ ግራ ተገባሁና ያጠፋሁ መስሎኝ ለቀቅኩት። ከመደናገጤ የተነሳ የተተኮሰባት ድኵላ መስልኩ። በኋላ ነገሩ ገርም አለኝና ሳላስበው ሳቄን አወካሁት። እጁን እያሻሸ፣ “ገና ሳምንት ትስቃለህ! ጀዝባ!” ብሎኝ ምንም እፍረት ሳያሳይ እየተጀነነ አንዳንዴም ዞር እያለ እየተገላመጠኝ መንገዱን ቀጠለ። ያ ዓይን አውጣ ሌባና ወያኔዎች አንድ ናቸው። ወያኔዎቹ ባይብሱ! በነገራችን ላይ ወያኔና ዱሩየዎች አብረው እንደሚሠሩ ታውቃላችሁ? እጅና ጓንት ሁነዋል። ሰም ማጥፋት እንዳይመስላችሁ። ዕውነቴን ነው። በሌቦች ተባባሪዎቻቸው አማካኝነት ነበር የፕሮፌሰር አስራትን (ነብሳቸውን በገነት ያኑርልን) ቦርሳ አስነጥቀው በውስጡ የተገኘውን ሰነድ ምንም ሳያፍሩ በጋዜጣቸው ያስወጡት። የጋዜጠኛው ማስታወሻ ደራሲ ተስፋዬ ገብር አብ ይጠየቅ። የኢሰመጉን ቢሮ በዱሩዬዎች አሠብረው ንብረትና ሰነድ እንዳሰረቁ አንድ የኮበለለ የፓሊስ መኰንን ከነመረጃው ለዓለም አጋልጧል።
አገር ቤት ያጧጧፉትን ማጭበርበር ውጭ አገርም ተያይዘውታል። ማጭበርበሪያ ዘዴአቸው በየጊዜው ይለዋወጣል። አንድ ሰሞን በየኤምባሰው የቅጥረኛ ወኪሎቹ አማካይነት ስደተኛውን ሁሉ አዲስ አበባ ውስጥ የከተማ መሬት እንሰጣችሁአለን፣ ኑ ተደራጁ ብለው ልባቸው ውልቅ እስኪል ስበኩአቸው። ይኸን የጠላት ቅጥረኛ ለመታገል ቆርጠን የተነሳን ስደተኞች ወንድሞቻችንና እህቶቻችንን ለማስጠንቀቅ ያደረግነው መሯሯጥ በወያኔ አፍዝ አደንግዝ ድግምት ከሸፈብን። አባሻ ሆዬ ተንጋግቶ ገባለት። የከተማ መሬት በአቋራጭ ተግኝቶ! የወያኔ ባለሟሎች ያንን ሁሉ የስደተኛ አድራሻ ሰብስው፣ “ያውላችሁ፣ ኢትዮጵያውያን ተበደልን ብለው ጥገኝነት ይጠይቃሉ፣ ዳሩ ግን ከአንዳንድ ጽንፈኞች በስተቀር አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ከኛ ጋር ተባብሮ ይሠራል” በማለት የብዙ ሺ ሰዎች ስምና አድራሻ ለየመንግሥታቱ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር መሥሪያ ቤቶች አስረክቡ። ለዕውነትኛው ደጋፊአቸው የተወሰኑ መሬቶችን ሰጥተዋቸው፣ የተቀሩትን፣ “ሥጋ የለም መረቅ ጠጡ” ብለው ሸኙአቸው። ያስያዙትም ገንዘብ እንዳለ ውሀ በላው።
ቀጥለው ሁለተኛ ዙር እቅዳቸውን አንድግበው ብቅ አሉ። “ኑ! ንዋያችሁን አገር ቤት አፍስሱ” (investment) ብለው ውጭ አገር ነዋሪ ኢትዮጵያውያንን ጋበዙ። አንዳንዱ አላዋቂ የዋህ አገሩን የረዳ መስሎት፣ “እምን አካባቢ ንዋዬን ላፍሥ (invest) ብሎ ምክር ጥየቃ ገባ። ለዚሁ ጉዳይ የሰለጠኑ ምላሳቸው ጥሬ ይሚቆላ ካድሬዎች መንግሥት የእርሻ መሬት እንደሚሰጣቸውና፣ አበባ ተክሎ ወደ ውጭ መላክ እንደሚያዋጣና ተወዳዳሪ የማይገኝለት የትርፍ ጥገት መሆኑን አሳመኑአቸው። ተደራጁ ተባሉ። ገንዘብ ሰብስቡ ተባሉ። ጅሎቹ እንደተባሉት አደረጉ። ቱጃር የመሆን ሕልማቸው ግን ወያኔ ገንዘባቸውን እኪሱ ከከተተ በኋላ፣ ደብዛው ጠፋ። መሬቱም አልተሰጣቸው፣ አበባውም አላበበ፣ ገንዘባቸውም አልተመለሰላቸው። እዬዬ ቢሉ ማን አዝኖላቸው?
ሶስተኛው ዙር ዕቅዱ በሚሌኒየም ሳቢያ ሚልዩን በሚሊዮን ዶላር ሐይቅ ሊዋኙ የነደፉት ነበር። ከየአንዳንዱ ሚሌኒየም ኢትዮጵያዊ ቱሪስት ቢያንስ ቢያንስ አንዳንድ ሺ ዶላር ሊመነትፉ ተመን አውጡ። የለየላቸው ቁጭ በሉዎች ከሎንዶን ኢምፖርት አደረጉ (ወደ አገር አስገቡ)። ይኽ ዝግጅት የ፲፱፻፺፯ ምርጫን ተከትሎ የጨፈጨፉት የንጹሐን ደም ገና ቀለሙ ከአስፋልቱ ላይ ሳይለቅ ነበር። የቅንጅት መሪዎች “በአገር ክህደት ወንጀል” ተከሰው ወህኒ ታጉረዋል። አንዳንድ ሞኛሞኝ ወገናችን በአፍዝ አድንግዞቹ ድግምት ተታሎ ሊቀላቀላቸው ስንቅ ሲሰንቅ ደርሰንበት፣ ኡ ኡ ብለን ጮኽንበት። “ጥቁር ውሻ ውለድ” ተብሎ ተገጠመበት። አብዛኝው ኡኡታችንን ሰምቶ ጉዞውን ቢሰርዝም፣ ሌሎቹ፣ ገንዘባቸውን ቋጥረው፣ በብዙ ዋጋ የአይሮፕላን ቲኬት ገዝተው “አፍንጫችሁን ላሱ” ብለውን ገቡ። መለስ ዜናዊ ከነሚስታቸው (ውይ ምስኪን!! ሲያሳዝኑ! ኑሮ “ቀዳማይ” እመቤት አዜብ መስፍንን እንደሚያገላታቸው አያችሁ?) በሱዳንኛ ሲደንሱ በቴለቪዢን መስኮት ከማየት በስተቀር ያገኙት አንዳችም ፋይዳ አልነበረም። ለንዶን ላይ ያደረግነው አከባበር እትዮጵያ ውስጥ ከተደረገው ይበልጥ ኢትዮጵያዊ ደርዝ (style) ነበረው።
እኔ የሚገርመኝ፣ የሚታለል ሕዝብ ብዛቱ! ተታሎ! ተታሎ! ተታሎ አለማለቁ! አንዱ ተሞሽልቆ ሲውጣ በብረት ዓይኑ እያየ ሌላው ሊላጭ መግባቱ! ሰሞኑን ጆሮን ጭው ከሚያድረጉት ውስጥ ለውስጥ ከሚሽሎከሎኩት ዓበይት ጉዳዮች መሐል፣ የይሉኝታ ሽታ (DNA) ዝር ያላለበት የዘመናችን ዓይን-አውጣ ቡድን በየትላልቅ የዓለም ከተሞች በወኪሎቹ አማካይነት የሚያደርገው የገንዘብ ፍለጋ መልከስከስ ነው። አሁንስ ብሶበታል። ኢትዮጵያ ውስጥ የሚንቀሳቀሱት የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች፣ የሙያ ማኅበራት፣ ተቃዋሚ የፖሊቲካ ድርጅቶች ምንም ዓይነት የገንዘብ ዕርዳታ ከውጭ እንዳይደርሳቸው ሕገ-አራዊት ነድፎ አንቀጽ ቋጥሮ ጥርቅም አድርጎ በሩን ዘግቶባቸዋል። ይኸን ካደረገ በኋላ የራሱን የልመና ኮሮጆ አንጠልጥሎ፣ ያለምንም ሀፍረት በዓለም አቀፍ መንግሥታዊ ድርጅቶች ድጃፍ “ስለ-እመብርሀን” መጽውቱኝ፡ኢያለ ልመናውን በሞኖፖል ተያያዘው። ታዲያ ምን ያረጋል፣ ቢሯሯጥም ቋቱ ጠብ አላለለትም። በሌላ በኩል ደግሞ፣ “አሁን በሌሎች በሩን ሰለጠረቀምኩት፣ ወጭ ያለው ኢትዮጵያዊ ለሎችን መርዳት ስለማይችል፣ ገንዘቡን ለኔ የሚያስረክብበትን ዘዴ ልቀይስ” ብሎ የተነሳ ይመስላል። ጨዋ ለመምሰል መጀመሪያ በዓይጋና በዋልታ የመረጃ ማዛቢያ ድረ-ገጾች ላይ ኢትዮጵያውን “ዶለራችሁን፣ ፓወንዳችሁን፣ የናችሁን እንዳለ በአገራችሁ ባንክ ማስቀመጥ ትችላላችሁ” ብሎ አወጀ። የሰማውም የለ። መልሳችሁ መውሰደም ብትፈልጉ በዚያው ባስቀመጣችሁት አገር ገንዘብ (currency) ይሰጣችሁአል” እያለ ወተወተ። ማን ሰምቶት! እነዚያን ድረ-ገጾች የሚያነብ ኢትዮጵያዊ በቁጥር ኢምንት ነበርና አመርቂ ውጤት አልተገኘም። ለ ዲ ኤል ኤ ፓይፐር በየወሩ 50 ሺ ዶላር ከየት መጥቶ ይከፈል? ጉድ ፈላ። ወያኔ ኤምባሲ ለተለያየ ጉዳይ የሚሄዱትን “ጠቃሚ መረጃ” እያለ ይጠቁማቸው ገባ። አልሆነም። አሁን ግን ነገሩ ዓይኑን አፍጦ መጣ። በታወቁት የወያኔ ቅጥረኛ አውደልዳዮች (ካድሬ) እና ለንዶን ውስጥ ከሚኖሩት፣ እነዚያ ዓባይ ሜዲያ ድረ-ገጽ “ወያኔ! ወያኔ! ወያኔ” እያለ ታርጋቸውን ግምባራቸው ላይ በለጠፈባቸው ሆድ አደር ከርሳሞች አማካይነት ያንኑ ዓይጋ ድረ-ገጽ ላይ ያያችሁትን ፎርም በገፍ እያባዛ በየሬስቶራንቱና በየመሸታ ቤቱ እያስዞረ መከፋፍል ጀምሯል። አልሰሜን ግባ በልው!! ሆ ሆ ይ! ጥጃ ለጅብ አደራ ይሰጣል እንዴ! ገንዘቡን መጣያ ያጣ ኃብታም ካለ ደግ።
እንግዲህ ወያኔ የማጭበርበር መሣሪያውን ወልውሎ በመጣ ቁጥር ከማስጠንቀቅ በሻገር የምናደርገው ነገር አይኖርም። ከዚህ በፊት ተናግረናል። አስጠንቅቀናል። “እምብየው!” ብለው ሂደው ተበሉ። አሁንም ይኸውና አዲስ ዘዴ አንግቦ ሊያጭበረብራችሁ ተነስቷል። አሁንም አዳሜ፣ “እምቢ” ብለሽ ሂደሽ የእሳት ዕራት ከሆንሽ፣ እኛ የምንለው፤ “ወደሽ ከተደፋሽ ቢረግጡሽም አይክፋሽ” ነው። እሰየው ከማለት ባሻገር ከንፈር የሚመጥላችሁ እንደማይኖር ከወዲሁ ዕወቁትና ጥጃችሁን ለጅብ በአደራ ከማስረከብ ታቀቡ።

Saturday 1 May 2010

ቀደዱ እንጂ አልዋሹም!

ከወንድሙ መኰንን

የወያኔ የሹመት ክፍታ የሚለካው በሚዋሽ ምላስ ርዝመት መሆን አለበት። ለዚህ ይሆናል የወያኔ ተሿሚዎች ዓይናቸውን በጨው ሙልጭ አድርገው ታጥበው ሽምጥጥ አድርገው በውሸት እርስ በርስ የሚወዳደሩት። መቸም እራሳቸውን ካልሆነ ማንንም እንደማያሞኙ ግልጽ ነው። በተላይ ዛሬ - ዛሬ ላይ የውሸት ችሎታቸው ኢየታየ መስል ለዲፕሎማሲ ከፍተኛ ሹመት የሚታጩት። ኧረ እባካችሁ ባህልና ጨዋነት ገደል ገብቷል፣ የሕሊና ያለህ!!!!

ከዚህ በፊት፣ ረቡዕ ሐምሌ ፲፩ ቀን ፩፱፻፺፱ ዓ. ም. ወያኔ ወገኖቻችንን ጨፍጭፎ ካበቃ በኋላ የተቃዋሚ መሪዎችን ሰብስቦ እስር ቤት አጉሮ፣ “ሕገ-መንግሥቴን ስላላከበራችሁልኝ፣ እኔን በድምጽ ብልጫ ከዙፋኔ ልታነሱኝ ስለተነሳችሁ ዕድሜ ይፍታችሁ!” ብሎ በሚቆጣጠረው ፍርድ ቤቱ በመፍረዱ የተናደዱ ፲፪ ኢትዮጵያውያን በቀጥታ ገስግሠው የሎንደኑን ኤምባሲ ቁጥጥር ሥር አዋሉት። አንድ ሰዓት ሙሉ ኤምባሲውን ተቆጣጥረው እንግዳ መቀበያ አዳራሹ ውስጥ ያሉት ግድግዳዎች በተጨፈጨፉት ወገኖቻችን ፎቶግራፎች ለጣጥፈው ጥርት ባለ ሰማይ ላይ ርጭት ያሉ ክዋክብት አስመሰሉአቸው። የሚገባውን ሁሉ ተስተናጋጅ ተቀብለው፣ ወያኔ የሚፈጽመውን ወንጀል አንድ በአንድ አስረዱ።

የጀርመን ሬዲዮ በቀጥታ በስልክ ከቦታው ይደረግ የነበርውን ቀድቶ ለሕዝባችን አሰማ። የወያኔ ተላላኪና ጉዳይ አስፈጻሚ ብርሀኑ ከበደ በቦታው አልነበሩም። ሠራተኞቹ ተደናግጠው እንግዳ መቀቢያውን ለተቃዋሚ ሰልፈኞቹ ጥለውላቸው አንደኛው ፎቅ ላይ ዘግተው ፖሊስ ጠሩ። ፖሊስ ደርሶ ወንድሞቻችን ምን እያደረጉ እንደሆነ ጠየቁአቸው። እነሱም አምባሳደሩን ለማነጋገርና ለምን እንዲህ ዓይነት ወንጀል በአገራቸው እንደሚፈጸም ለመጠየቅ መጥተው እንዳጡአቸው አስረዱ። ፖሊሶቹም “በቃ አሁን መልዕክታችሁን በሚገባ ሁኔታ አስረድታችኋል። አሁን ሂዱ” በለው ተማጽነዋቸው ኢትዮጵያውያን ወደየቤታቸው ከአንድ ሰዓት ቆይታ በኋላ አሰናበቱአቸው። ማታ የጀረመን ሬዲዮ ያቀናበረውን አስተላለፈ። የተቃጠለው የሕዝባችን አንጀት ትንሽም ብትሆን በነዚህ ቆራጥ ወገኖች በወሰዱት እርምጃ ራሰ።

ቀጣሪ ጌቶቻቸው ከአዲስ አበባ ደውለው ወረደውባቸው ነው መሰል፣ አባሳደር ብርሀኑ ከበደ ምንም ሳያፍሩ፣ ወደ ጀርመን ሬዲዮ ቢሮ ደውለው “ውሸትን ዕውነት አስመስላችሁ እንዴት ታስተላልፍላችሁ። አንድ ሁለት ቦዘኔዎች ከሕዝቡ ተቅላቅለው እምባሲ ውስጥ ገብተው ነበር። አምስት ደቂቃ ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ተገፍትረው ወጥተዋል። እንዴት ያንን ወሬ ብላችሁ ታወራላችሁ ብለው” አምባረቁቸው። የጀረመን ሬዲዮም ዕድሉን ሰጥቶአቸው በሚቀጥለው ቀን ውሸታቸውን እንዲቀዱት ፈቀደላቸው። መቸም ጆር አይሰማ በዚህ ዕድሜአቸው ሲቀዱ ሰማንላቸው። “ስጥ እንግዲህ!” ይላል አራዳ ልጅ። ይኸ ጸሐፊ ወንድሞቻችን ኤምባሲውን ከተቆጣጠሩት ሰዓት ጀምሮ እስከለቀቁ ደረስ ሁኔታውን ይከታትል ነበር። ልጆቹ የሠሩት ጅግንነት ከምንም በላይ ሊዘገብ ቢችልም ዝም ብሎ አልፎት ነበር። የአምባሳደሩን ቀደዳ ከሰማ በኋላ ግን “የምጣዱ እያለ የዕንቅቡ ተንጣጣ” በሚል ርዕስ በዕውነት የሆነውን በቪዲዮ “መቅረጸ-ስዕል” ተጨባጭ መረጃ አሰደግፎ አምባሳደር ተብዬው ያሉት በሙሉ ውሸት መሆኑና ሂሊናቸውን ሽጠው የሆነውን አልሆንም እንዳሉ አስቀመጠላቸው። ጽሑፍ አንብበው፣ ቪዲዮውን አይተው ካበቁ በኋላ አምባሳደር ሆዬ እዬዬአቸውን አቀለጡት። ሎንዶን ሜትሮፖሊታን ፖሊስ ጣቢያ ሩጠው ሂደው “እሪ አለቅን! ሕግ ባለበት አገር ሕገ-ወጥ ቦዜኔዎች በጉልበት ኤምባሲአችንን ያን ሁሉ ሰዓት ሲቆጣጠሩት አንድ ሰው እንኳን እንዴት አላሰራችሁም። የዲፕሎማቲክ ጥበቃችሁ ተጓደለብን፣ የኢትዮጵያና የእንግልዝ ወዳጅነት በዚሁ ጉዳይ ሊያከትም ነው። አንድ ነገር አድርጉ። ይኸው ከአንድ ሰዓት በላይ በሰላም ለመሥራት ዋስትና የለንም። ዛሬ ያለምንም ችግር ኤምባሲውን ተቆጣጥረውት ከሄዱ ነገ መጥ|ተው ላይገድሉን ምን ዋስትና አለን ... “ ገለመሌ አሉ!! “ቪዲዮውን እዩት!! አልቀናል! እንዴት ዝም ትላላችሁ!” በማለት በዚያው በጀርመን ሬዲዮ “ሁለት ሰዎች፣ አምስት ደቂቃ” ባሏት አፋቸው መልሰው ፖሎሶች ላይ አለቀሱባቸው። ፖሊሶቹም ይሄንን ድርገት መርቷል ያሉትን አንዱን ወንድም ጠርተው፣ የውያኔውን አምባሳደር ዕንባ ለመጥረግ ያህል፣ አስጠነቀቁት።

የወያኔው ተላላኪ፣ አምባሳደር “ብርሀኑ ከበደ” ከዚያ ትምህርት ወስደው “ሳይገድሉ ጎፈሬ፣ ሳያረጋግጡ ወሬ” እንደማይደግማቸው ተስፋ አድርገን ነበር። ዳሩ ምን ያደርጋል አሁንም ደገሙት። ያሁኑ ይባስ!!! ያሁኑ ይባስ!!! ወይ ቅሌት!!

ሰኔ ፱ ቀን ፪ሺ፩ ዓ. ም. ኢትዮጵያውያን የወያኔ መንግሥት የሚያደርሰውን ጭፍጨፋ፣ ጠቅላላ የሰባዓዊ መብት ገፈፋ፣ እና ዓይን ያወጣ ንቅዘት ወይም ሙስና፣ ብርቲሽ የተመራጮች ምክር ቤት አባላት፣ ለበጎ አድራጎት ድርጅት አባላት፣ ለትብብር ከውሦስተኛው ዓልም ሕዝብ ጋር (Solidarity with the Third World) አባላት እና ለጋዜጠኞች ሶስት ሰዓት የፈጀ ገለጻ በሀውስ ኦፍ ኮመንስ በሚባለው የተመራጮች ምክር ቤት (House of Commons) አቅረበው ነበር። ገለጻው የብዙዎችን ዓይን የከፈተ እና ብዙዎቹ ጉድ ያሉበት ነበር። ይኸንን ከፍተኛ ስብሰባ በዓይነቱ ልዩና የመጀመሪያው በመሆኑ፣ አዘጋጆቹን ቪኦኤ በመባል የሚታውቀው የአሜሪካን ድምጽ ሬድዮ እና የጀርመን ሬዲዮ አዘጋጆቹን አፈላልገው ቃለ መጠይቅ (interview) አድርገው ነበር። ይኸ ሁኔታ ውያኔን ከምንም በላይ አስደነገጠው። የሚይዙትን የሚጨብጡትን ያጡት ለማጁ የወያኔ ተላላኪ ቦቦታው ሳይኖሩ፣ ለአሜሪካን ድምጽ ሬዲዮ ዓይን ያወጣ የውሸት ስልቻቸውን እንደገና ደገሞው ቀደዱት።

“በመጀመሪያ ደረጃ፣ እንዲህ ዓይነት ስብሰባ አልነበረም፣ የነበረው ትብብር ከሶስተኛው ዓልም ሕዝብ ጋር (Solidarity with the Third World) በቅርቡ ገንዘብ ለማሰባሰብ ያደረገው ቅደመ ስብስብ ነበር። አንዲት ሳብራ የምትባል ሴት እነዚህ ተቃዋሚ ነን የሚሉ ሰዎች በጎን ጠራርታ አመቻችታላቸው ነው የገቡት”

በማለት አጥላልተው፣ አወዳድቀውና አቃለው ለማለፍ ሞክረው ነበር። ጋዜጠኛው “እንደስዚህ ዓይነት ስብሰባ አልተደረገም ነው የሚሉኝ?”ብሎ ሲያፋጥጣቸው፣
“አይ አልተደረገም አላልኩም። የኢትዮጵያን ጉዳይ ለመነጋገር የተጠራ ስብሰባ አልነበረም። እኛ አልተጋብዝንም። ስብሰባው ተደርጓል ግን በትንሽ ክፍል 14 ቁጥር ውስጥ የተደረገ አነስተኛ ስብስባ ነበር። አንድም የፓርላማ አባል አልነበረም”

በማለት ዘባርቀዋል። ውሸታቸው ያሳፈረው ጋዜጠኛ አዲሱ አበበም ግርም ብሎት፣ “የተከበሩ ብሩስ ጆርጅ አልነበሩም ነው የሚሉኝ” ሲላቸው፣ ድንግጥ ብለው “አይ ለትንሽ ደቂቃዎች ነበሩ። ትንሽ ካዳመጡ በኋል ውልቅ ብለው ወጥተዋል” በማለት ሽምጥጥ አድረገው ሳያፍሩ ክደዋል። “አይነጋ መስሏት” ነው አበው የሚሉት?

በመጄሪያ ደረጃ፣ ስብሰባው የተደረገው፣ ኢትዮጵያው ውስጥ ለሚደረገው አፈናና ጭቆና ለአገሪቱ ፓርላማ፣ በጎ አድራጎት ድረጅቶች፣ ሰብዓዊ መብት ድርጅቶች፣ ትብብር ከሦስተኛው ሕዝብ ጋር እና ለጋዜጠኞች ታስቦ የተደረገ እንጂ ለገንዘብ ማሰባሰቢያ ቅደመ ዝግጅት አልነበረም። “ወሸት ቁጥር አንድ” በሉ! ፲፬ ቁጥር ክፍል አነስተኛ በመሆኑና የሚመጡት እንግዶች ከሦስት መቶ በላይ በመሆናቸው፣ ከዚያ ባሻገር ወያኔ የፈጸማቸው የዘር ማጥፋት ቪዲዮና በሙስና የተዘፈቀበት መረጃ በፕሮጀክተር ስለሚቀርብ ስብሰባው የተደረገው በታላቁ የኪሚቲ ስብሰባ አዳራሽል (The Grand Committee Room) ነበር። ውሸት ቁጥር ሁለት በሉ። አንድም የፓርላማ አባል የለም ብለው ዓይናቸውን በጨው አጥበው ለሸመጠጡት፣ ጉባዔውን የከፍቱት በክብር እንግድነት የሁሉም ፓርቲዎች የምክር ቤት ሊቀመንበር፣ የተከበሩ ዴቪድ አንደርሰን (The Chairman of All Party Parliamentary Group on Third World Solidarity, MP David Anderson) ነበሩ። ውሸት ቁጥር ሦስት በሉ! አምባሳደር ተቢዬው ሲወጠሩ ተውናብደው አንደርሰን ብቻ ተገኝተው ነበር። ውሸት ቁጥር አራት! አንደርሰን ብቻ አለነበሩም። ከመኖርም አልፈው የመዝጊያ ንግግር ያደረጉት የተከበሩ ብሩስ ጆርጅ ነበሩ። ውሸት ቁጥር አምስት። አንድም ጋዜጠኛ አልነበርም ላሉት፣ “ተመክሮና የአሁኑ የሜዲያ ሽፋን በኢትዮጵያ (Exeprience and The Current Media Coverage in Ethiopia) በሚል ርዕስ ንግግር ያደረገችው ታዋቂዋ የጋርዲያን (The Guardian) ጋዜጣ ዘጋቢ ሳውንድራ ሳተርሊ (Saundra Satterlee) ነበረች። ውሸት ቁጥር ስድስት! በስንት ፍጥጫ የተከበሩ ብሩስ ጆርጅን መገኘት ያመኑት አማሳደር ብርሀኑ (ምኑን ብርሀን ሆኑ)፣ ብሩስ ጆርጅ አቋርጠው ሂደዋል ላሉት፣ የመዝጊያ ንግግራቸውን ሲያደርጉ፣ “If there were a contest in the severity of corruption the rulers of Ethiopia, who have redefined the word, would undoubtedly win the gold prize.” (በሙስና ዝቅጠት ውድድር ቢደረግ፣ የቃሉን አዲስ ፍቺ ያገኙልን የኢትዮጵያ መንግሥት መሪዎች፣ የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊ ሁነው ባጠለቁ ነበር) በማለት ተሰብሳቢውን አስቀውታል። ከዚያም አልፈው ተርፈው በመጨረሻ የዚህን ጽሑፍ አቅራቢ ውጪ ጠብቀው ወደ ጎን ወስደውት አንዳንድ ነገሮቻን ካወያዩት በኋላ ወደፊት ተገናኝተው በሰፊው መረጃ መሰብሰብ ላይ አብረው ለመሥራት ወስነዋል።

ተወካይ አልላኩም ላልቱ ጭልጥ ላለ ቅጥፈት፣ በመጀመሪያ ደረጃ እሳቸው በቦታው አልነበሩም፣ ታዲያ ማን መረጃውን አጥናቀረላቸው? እልፍኝ አስክልካያቸው ሆድ-አደር ያለው ከበድ እዚያ ጉጉት መስሎ ጉልት ብሎ አላመሸም? እንዲያውም አይታው ብግን ያለች አንድኛዋ እህታችን፣ “እምባሲ በር ይዞ አትገቡም እያለ ዘበኛ ይመስል ፍርፋሪ ለቃሚ የወያኔ እልፍኝ አስከልካይ ምንድነኝ ብሎ ነው እዚህ የተጎለተው? ወይ አያምር ወይ አያፍር!” ብላ የዚህን ጽሑፍ አቅራቢ አስቃዋለች። ያስ ሌላው ተላላኪአቸው? ዓለማየሁ ነኝ ያለው (ዓለሙ ጥፍት ትበልበትና)! አንዷ እህታችን “ዶማ” ያለችው! ስለወያኔ ሙስና በቀረበው በዚያው መድርክ፣ “ይኸ መንግሥት ብዙ ለውጥ አምጥቷል። ብዙ ወጣቶችን ባለመኪና አድርጓል” ብሎ ሲናገር ሕዝቡስ ጮሆበት አፉን አላስዘጋውም? ሚዛናዊ አይደላችሁም ብሎ ለመናገር ሲሞክር፣ አንዳዶቹ በጣም ከመናደዳቸው የተነሳ “የት ያለህ መሰለህ? የኢትዮጵያ ፓርላማ?” እያሉ ይጮኹብት የማን መልዕክተኛ ነበር?

በቦታው የነበሩ አንድ የቀድሞ የዲፕሎማቲክ ከፍተኛ ባለሥልጣን የቪኦኤውን ትርተራ እንዳዳመጡ፣ ለዚህ ጽሑፍ አቅራቢ ደውለው፣
“ብርሀኑ ከበደ፣ የዲፕሎማሲን ሙያ አዋረደ። ሁላችንም ድፕሎማት ነበርን። የአገርን ጥቅም ለማስከበር የስብዕናን ክብር ሳያዋርዱ መሥራት ምንም ነውር የለበትም። ግን እንዲዚህ መቀደድ ያሳፍራል። ቤልጀይም ጁኒየር ድፕሎማት ሁኖ ሲሠራ ደህና ወጣትና ወደፊት ጥሩ ባለሟል ይኾናል ብዬ ስጥብቅ ነበር። እንዲህ ዓይነት ወራዳ ሥራ ሲሠራ በማየቴ አዘንኩ”
ብለዋል።

አምባሳደር ብርሀኑ ከበደ፣ ቤልጀየም በነበሩብት ጊዜ የደርግ ጥቅም አስጠባቂ ነበሩ። እሱስ ይኹን፣ ያን ጊዜ የደርግን መንግሥት ያገለግሉ የነበሩ፣ ሥርዓቱ ሲወድቅ፣ መጪው መንግሥት አገር ጎጂ በመሆኑ እንዳለ ተሰደዋል። ክፍተት ሲገኝላቸው ሰልፋቸውን አስተካክለው አምባሳደር ተባሉ፣ ያውም የወያኔ! አምባሳደር ብርሀኑ! ሞኝ አይሁኑ! ትንሽ እንኳን የኢትዮጵያ ሕዝብ ይቅር እንዲልዎት እንዲህ ዓይነቱን የወራዳ ሥራ እራስዎ አይስሩ። የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ኃላፊ የለዎትም? እሱ ወጥቶ ይቀላምድ። እርስዎ ምን በወጣዎት! እንዲይ ዓይነቱን መቅደድ ለቦታው የተዘጋጀ ሰው ይቀደደው። ልብ ይበሉ። ይኸ ምክር የወዳጅ ምክር ነው። ይልቅ እስዎ ወያኔ አይታመንም እና ልክ እንደ ፍሰሀ አዱኛ በጊዜ ሹልክ ብለው ያምልጡ። ይሻልዎታል። ለምን ቢሉኝ፣ ጌታዎ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሥቃይ፣ መለስ ዜናዊ ብለው ጨርሰውታል። ጠቅላይ ሥቅዩ ምን አሉ መሰሰዎት!

“የወያኔ ሹመት የዛፍ ላይ እንቅልፍ ነው። ሽልብ ካሉ ዱብ ነው።”

ማንም አምባ ገነን መንግሥት ሥልጣንን ሙጭጭ ብሎ ለዘልዓለም ጨብጦ የኖረበት ታሪክ በአገራችንም ሆነ በሌላው ዓለም ታይቶ አይታወቅም። ሁሉም አምባገነን ሌሎቹን እንዳዋረደ እሱም በተራው ተዋርዶ ከሥልጣን ይወርዳታል። አብዛኛው የአምባገነን ከነግሳንግሱ ለሌሎች ባዘጋጃት ወጥመድ እራሱ ይገባባታል። ከቀናውም ለስደት ይዳረጋል። እንደርስዎ ላሉት ለጀሌዎቹ ወይውላቸው። ወያኔ የኢትዮጵያውያንን ቆሽት አሳርሮ አይኖራትም። አምባሳደር ብርሀኑ! በሰፈርዎ የዕውነት ብርሀን ደብዛዋ እንደ አዲስ አበባው መብራት ጠፍታለች። አሁንስ ጨለማው ከበደ።