Friday, 17 October 2025

ሕዳሴ ግድብ፣ ዓባይ፣ ኦርቶዶክሳዊት

                                                   ሕዳሴ ግድብ፣ ዓባይ፣ ኦርቶዶክሳዊት

ቤተ ክርስቲያን:-እሬትና ማር

ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ

nigatuasteraye@gmail.com 

 

ጥቅምት ፮ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም.

(October 16, 2025)

መግቢያ

ኢትዮጵያ ያቋረጠቻቸው ረዥም ዘመናት በውስጣቸው ያሉት ዓመታት፣ ወራትና እለታት የሚገጥሟቸውን ክስተቶች እየደመሩ የሚሽከረከሩባት እንዝርት ናት፡፡ እየተሽከረከሩ በመስከረም ወር ላይ በሚገጥሙት ዓውደ ዓመት የሚታወሱ በዓለት ድርብርቦችና ድምሮች ናቸው፡፡ የመደመር ባህላችንን ተከትሎ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ደቱን ለመቀጠል ለመጀመሪያ ጊዜ በደመራ ላይ ተደምሮ ብቅ አለ፡፡

በሰውነታችን ውስጥ ያሉት ሴሎች እያንዳንዳቸው የትዝታ መዛግብት እንደሆኑ፡ በኢትዮጵያ ታሪካዊ የሕይወት ጉዞ እያንዳንዳቸው ቀናት የትዝታ መዛግብት ናቸው፡፡ በዚህ ምክንያት ድርብ (ድምር) እንጂ ነጠላ በዐል የልንም፡፡ ኢትዮጵያ ባቋረጠችትባቸው ዘመናት እስከ ግድቡ ፍጻሜ ድረስ ከመሰቀሉ በዐል ሌሎች በራሱ በደመራ ላይ የተደመሩ ከዓባይ ራቅ ላለው ሕዝብ ያልተገለጹ ብዙ ክስተቶች አሉ፡፡

ኢትዮጵያ ክመከስቷ በፊት የነበረና ኢትዮጵያ ከተከሰተችበት ዘመን ጀምሮ በወገቧ እንደ መቀነት ተጠምጥሞ ይኖር የነበረው ዓባይ፡ እስከ ዓለም ፍጻሜ ሲከበር የሚኖረውን ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ደምሮ በዚህ ዓመት ተከሰተ ፡፡ የወገቧ መቀነት ሆኖ የኢትዮጵያ ሽንጥና ዳሌዋ ሲታይባት የኖረውና የማንነቷ መነበቢያ አትሮኑስ ሆኖ የኖረው ዓባይ የኢትዮጵያን ባሕርይ ቀይሮ እያስነበበ ብቅ አለ፡፡

ባዓባይ ሲገለጽ የኖረው የኢትዮጵያ ውበት ይነበብበት (ይገለጽበት) የነበረው አትሮኑስ ጎጃም ነው፡፡ “ውሀን ከምንጩ፣ ነገርን ከሥሩ እንዲሉ” ጎጃም ደስታውንም፣ ሐዘኑንም፣ ስሜቱንና ሁለመናውን የሚገልጸው በአባይ ወንዝ (ናይል) ነው፡፡ ስነ ጽሑፉ ግጥሙና ቅኔው ሁሉ የሚመነጨው ከዚያው ነው፡፡ ኢትዮጵያ ከመከሰቷ በፊት ጀምሮ ግድቡ እስኪፈጸም ድረስ ስለ አባይ የቀረቡት ቅኔወች ፉከራወችና ግጥሞች ብዙ ናቸው፡፡ ሁሉንም አምቆ በመሸከም ሲፈስ የኖረው የዓባይ ግድብ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲከበር የቀረበው ቅኔ በጎጃም ሊቃውንት ሲታሰብ ስድ ንባብ ሆኗል፡፡ 

የቀረቡትን ስድ ንባቦች ባደግኩበት የቅኔ ስልት ፈተሽኳቸውና ስሜቴን ዳሰሰኩት፡፡ ካንድ ወጃጄ ጋራ የተላለፉትን ግጥሞች አንስተን ተነጋገርንና “አንተን በጎጃሙ ቅኔ ተቀኝ ቢሉህ እንዴት ትቀኝ ነበር?” ብሎ ጠየቀኝ፡፡ “እንዴት ትቀኝ ነበር?” የሚለው ጥያቄ፦ ባንድ ወቅት ካነበብኳቸው መጻሕፍት መካከል ባንድ መጽሐፍ ያገኘሁትን ተመሳሳይ ነገር አስታወሰኝ፡፡ በነገረ መለኮትና በሰባዊ ተፈጥሮ ተማሪወች መካከል:- በወንድና በሴት መካከል ስላለው አካላዊና ስሜታዊ መሳሳብ ውይይት ተጀምሮ ክርክሩ ጦፈ፡፡ ክርክሩን እንዲዘጋ አንድ ሰው የመቋጫ ሐሳብ ተጠየቀ፡፡ የተጠየቀው ሰው “ከሳይንሱ ማሕጸን ገብቼ ስዋኝ የሴቱን ማሕጽን ረሳሁት እንጅ በወንድና በሴት መካከል ያለውን መሳሳብ ከኔ የበለጠ የሚገልጸው አልነበረም” ብሎ የሰጠው መቋጫ ትዝ አለኝ፡

የኢትዮጵያ ልጆች እርስ በርስ የሚተላለቁበት፤ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ አብያተ ክርስቲያናትና ገዳማት የሚቃጠሉበት፤ መነኮሳት ቀሳውስት ሕዝበ ክርስቲያን እየታደነ የሚገደልበት ዘመን ሆኖ በልቅሶና ዋይታ ላይ ተጣደንና ፋታ አላገኝንም እንጅ፦ ዐባይ በሚከበው በጎጃም ምድር ካልተወለደ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ተጠምቆ ካላደገ ሰው ሁለንተና ገላጭ የሆነ ቅኔ የሚጠበቅ አይመስለኝም፡፡ በተስፋ ሲጠበቅ የኖረው የዓባይ ግድብ ፍጻሜ ቢያስደስትም፡ ዓባይ ልጆች ላይ በመካሄድ ያለው ዘግናኝ ጭፍጨፋ  በመደመሩ ከጎጃም ሊቃውንት የሚፈልቀውን ቅኔ እሬትና ማር ያደርገዋል፡፡

ሆኖም “እንዴት ትቀኝ ነበር?” የሚለው ጥያቄ ጭንቅላቴን እረፍት ነሳውና መቁነጥነጥ ጀመረ፡፡ ኢትዮጵያዊት ቅኔ በድሮው አነጋገር በጨለማ በምትበራ ጧፍ ትመሰላለች፡፡ በዘመኑ አነጋገር በእጅ ባትሪም ልትገለጥ ትችላለች፡፡ የቅኔ ሰው ጧፍ ወይም ባትሪ ይዞ ወደማያውቀ ጨለማ ቤት የሚገባ ሰው ይመስላል፡፡ ባትሪ ወይም ጧፍ የጨበጠ ሰው ወደማያውቀው ጨለማ ቤት ሲገባ በቤቱ ውስጥ ተካቶ ያለውን ሁሉ ያያል፡፡ በጨለማው ተጋርዶ ማየት ለተሳነው ያሳያል፡፡ የቅኔ ሰውም በወቅትና በኩነቶች ተጠቅልለው ተፍታተው ለሰሚ ወዳልቀረቡት ሐሳቦች የሚገባው፦ ለማየትና ለመስማት ጉጉት ላለው ሰው ለማሳየትና ለማሰማት ነው፡፡ ለማየትና ለመስማት የሚጓጓ ሰው ከሌለ ለማነው የምቀኘው? ብሎ ማሰቡን ይተዋል፡፡ እኔም ! ይቅርብኝ! ብየ ልተወው ሞከርኩ፡፡

በኢትዮጵያዊው ቅኔ ስልት የተገራ ጭንቅላት ያየውን ላለመግለጽ አፍኖ መያዝ አይችልም፡፡ ከቁጥጥር ውጭ ይሆናል፡፡ እንዳልተገራ ግልገል ፈረስ ይቁነጠነጣል፡፡ በሚቁነጠነጠው ጭንቅላቴ በደመራ ላይ ተደምሮ ስለተከበረው የዐባይ ግድብ የቀረቡትን ግጥሞችና ስድ ንባቦች እንደገና ልቃኛቸው ግድ ሆነብኝ፡፡ ጠቅላይ ምንስቴር ዐቢይ አሕመድ በመደመር ርዕስ አቀናብረው በተደጋጋሚ ባቀርቧቸው መጻሕፍት ላይ በተለያዩ ተችወች የተሰጡትን የምርምር ትችቶችንም ሰማሁ፡፡ መጻሕፍቱን አግኝቼ ባላነባቸውም በጥልቅ ትኩረታቸው ያነበቧቸው ሰወች ባቀረቧቸው ትችቶች አማካይነት የመጻሕፍቱን መንደርደሪያ በመጠኑ ተረድቻለሁ፡፡ በጎጃሞች ላይ ለሚከሰቱት ደግና ክፉ አጋጠሚወች መገለጫና የስነ ባሕርያትም መተርጓሚያ ሆኖ በየደብሩና በየመንደሩ ሲነገሩ የኖሩ ናቸው፡፡ መደመርም በታሪካችን፣ በባህላችን በተለይ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያናችን እንግዳ አይደለም፡፡

የውጭ ወራሪና የውስጥ ተቀጣሪ ኢትዮጵያውያን በየዘመኑ ሲበትኗትና ሲከፋፍሏት አባቶቻችን መልሰው ሲገነቡባቸው ከነበሩት እሴቶቻችን መካከል መደመር አንዱና ዋናው ነው፡፡ ጠ/ ምንስቴሩ ነባራዊ እሴትነቱን ሳያሳዩ አዲስ ፍልስፍና አድርገው ማቅረባቸው እሴቶች እንዲዘነጉ ከተደረጉባቸው ብዙ አዘናጊወች አንዱ የሆነ ስለመሰለኝ በጠቅላይ ምንስቴሩ የቀረበው መደመር “እሬትና ማር” ሆኖብኛል፡፡ መደመርን ጠ/ ምንስቴሩ ከገለጹበት መንገድ ለየት ያለውን አዘግይቼ፦ በኢትዮጵያውያን እይታ ለማቅረብ ኢትዮጵያን ባጭሩ ገልጬ በሁለት ጡቶች ስለ ተገለጹት ስለ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንና ዐባይ ከዚህ በታች ለማቀረብ ሞክሬአለህ፡፡

 

ኢትዮጵያ


    አባቶቻችን የዓባይን ተፈጥሯዊ ቀዳሚነቱን ሳይረሱ በንግግራቸው ሁሉ ከዓባይ በፊት የሚያስቀድሟት ኢትዮጵያን ነው፡፡ ምሳሌ አርገው የሚከተሉት ጌታችን ክርስቶስ በተወለደበት ጊዜ በበረት የተከሰተውን ነው፡፡


የሰማይ ሠራዊት ከሰማይ የወረዱት መለኮቱን ተከትለው እንጅ ሥጋውን በመከተል አይደለም (ሉቃ 2፡13)፡፡ ምድራውያን እረኞችም ክርስቶስን በበረት ያዩት በሥጋው እንጅ በመለኮቱ አይደለም፡፡ የጥበብ ሰወችም ያዩት እመቤታችንና ሰውነቱ በግርግም ተኝቶ፣ ተጥቅልሎ ነው (ማቴ 2፡7-12)፡፡ 

የቀደሙ ሊቃውንት አባቶቻችን ምድራውያን እረኞችንና የጥበበ ሰወች ምሳሌ በማድረግ ከክርስቶስ በፊት የሚገልጿት ቅድስት ድንግል ማርያምን ነው፡፡ ይህን ምሳሌ በመከተል ዓባይ ከኢትዮጵያ ቀድሞ ቢታወቅም አስቅድመው የሚናገሩት ስለ ኢትዮጵያ ነው፡፡


እኔም ከዓባይ በፊት ኢትዮጵያን የሚገልጽልኝ ምሳሌ ስፈልግ “እናንት የኢየሩሳሌም ቆነጃጅት እኔ ጥቁር ነኝ ግን ከሁላችሁም የተዋብኩ ነኝ” (ማሕ 1፡5) እያለች በዐለም አደባባይ ራሷን ስትገልጽ የኖረችውን ኢትዮጵያን በማሕሌት ሲራክ ደምግባት አየኋት፡፡ እንደ ጠመኔ ያልገረጣ፤ እንዳረረ ከሰል ያልጠቆረ እንደ ጎመራ የወይን እሸት ከሩቅ በሚጋብዘው ደም ግባቷ ማሕሌት ሲራክ ኢትዮጵያን ገለጥችልኝ፡፡

በቅኔ ትምህርታችን ያለባለቤቱ ፈቃድ ሰውን መጥቀስ ይቅርና የሰውን ሐሳብ ሳያስፈቅዱ ከራስ እንደወጣ አርጎ መናገር ስሕተት ነውና የኢትዮጵያዊቷን ሱላማጢስ አባት ፈቃዳቸውን ጠየኳቸው፡፡

የማሕሌት አባት ኢትዮጵያንና ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያንን “አንች ውብነሽ በዐይነ ርግብ መሸፈኛሽ ውስጥ ዓይኖችሽ እንደ ርግብ ናቸው” (ማሕ 4፡1) እያሉ ሲያወድሱ ያደጉ ያቋቋም መምህር ናቸው፡፡ ለሚወዷቸው ለሁለቱም ለኢትዮጵያና ለቤተ ክርስቲያናቸው የሚያቀርቡትን ውዳሴ ከአብራካቸው በፈለቀችው ማህሌት የደመደሙ ያቋቋም መምህር የሰሎሞን ምክሼ ሲራክ ናቸው፡፡ “መኃልየ መኃልይ” ማለት የዜማወች መደምደሚያ የመጨረሻው ጽንፍ ማለት ነው፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን ካሉን ማሕሌቶች በላይ ስሜት የሚቀሰቅስ በእንቅስቃሴና ውዝዋዜ ተመስጦ የሚቀርብ አቋቋም የሚባለው ክፍል ነው፡፡ የማሕሌትን አባት የጠቀስኳቸው ማሕሌት ብቅ ስትል የማናት በሚል አነጋገሪያነቷ እንደማይቀርና ተመልሶ እንዳይመጣብኝ ለመግታት ብየ ነው፡፡ 

በማህሌት ሲራክ የገለጽኳት ኢትዮጵያ የአካሏ ቅርጽ እስከተዛባበት ስሟ እስከተዘነጋበት እስከ ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ዘመን ድረስ የነበሩት ጥንታውያን የቅኔ ሰወች አንች ሱላማጢስ “ቁመናሽ እንደ ዘንባባ ዛፍ መለል ያለ ነው፡፡ ጡቶችሽም እንደ ወይን ዘለላ ይመስላሉ”( 7፡8) እያሉ ሲቀኙላት ኖረዋል፡፡ ሻብያና ወያኔወች ቁመናዋንና ቅርጿን እስኪቀይሩባት ድረስ “እኅቴ ሙሽራየ የታጠረች የአትክልት ቦታ ዙሪያዋ የተከበበች ምንጭ የታተመችም ፏፏቴ ነሽ”(ማሕ 4፡12) እያሉ አወዳድሰዋታል፡፡ የቀርብ አባቶቻችን እነ ቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሤ፡ እነ መላከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬም “ሁለቱ ጡቶሽ መንታ እንደተወለዱ በሱፍ አበባ መካከል እንደሚሰማሩ እንደ ሚዳቋ ግልገሎች ናቸው” (ማሕ 4፡5) እያሉ ኢትዮጵያን የገለጹባቸው ቅኔወቻቸው በታላላቅ አድባራት በደብረ ኤልያስ፣ በዲማ፣ በብቸናና ደብረ ሊባኖስ ገዳም መምህራን እየተነገረን አድገናል፡፡

የሰባዊ ተፈጥሮን ውበት መግለጫ ሰምና ወርቅ ቅኔያችን የሚያስደንቅ ነው፡፡ በሚያስደንቀው ቅኔያችን የለሴቶችን  ወርቅነት የምንገለጻባቸው ሰሞች ብዙ ናቸው፡፡ ሴቶች በውርቅነት የሚገለጡባቸው በደረታቸው የበቅሉት ሁለቱ ጡቶቻቸው ናቸው፡፡ የኢትዮጵያን ቁንጅና ለመግለጽ ዓባይንና ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን በኢትዮጵያ ደረት ላይ የበቀሉ ሁለቱ ጡቶች ብለዋቸዋል፡፡ ዓባይና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በኢትዮጵያ ደረት ላይ የበቀሉ የማይነጥፍ ወተት በማምንጨት የማይነጥፈውን ተተካኪ ትውልድ የሚያጠቡ ናቸው፡፡

ከላይ እንዳልኩት ምንም እንኳ ዐባይ በተፈጥሮ ቀዳሚ ሆኖ ኢትዮጵያን ቢቀድማትም፦ ልጇ ከፈጠራት በኋላ ከሱ በሥጋ ቀድማ የታየችው ቅድስት ድንግል ማርያም ናት፡፡ በሰምና ወርቅ ቅኔያችን አባይንና ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያንን እያስከተልን ኢትዮጵያን በማስቀደም ሳንዳስሣት የምናልፋቸው እለቶችና ቅኔወች ጥቂቶች ናቸው፡፡

በመጽሐፈ መኃልይ ከሱላማጢስ ጋራ የተጠቀሱት ሶስቱ፦ ሚዳቋ፡ ግልገሎቿና የሚፈነጩባቸው የሱፍ አበባወች  የኢትዮጵያን ሁለንትና የሚገልጹ ናቸው፡፡ ኢትዮጵያ የሰው አገር እያደኑ በሚውጡት ቅኝ ገዥወች ተከባ መኖሯን ለመግለጽ  በአራዊት እየታደነች ምትበላዋ ሚዳቋ ሲገልጿት ኖረዋል፡፡ ግልገሎቿ የሚፈነጩባቸው የሱፍ አበበች የተባሉትም በዓባይ ተፋሰስ አካባቢ የሚኖረውን ተተካኪውን ትውልድ ይገልጹበታል፡፡ በሁለቱ ጡቶቿ ዐባይንና ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ይገልጿቸውል፡፡ አንዱ ጡት ጠልና ልምላሜ አመንጭ የሆነው ዓባይ ሲሆን፦ ሁለተኛይቱ የውበት መግለጫ  ቅኔ፤ ስነ ጽሑፍና ሙዚቃ ስታመነጭ የኖረችውን ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ናት ይላሉ፡፡

ሁለቱ ጡቶች:- ዓባይና ኦርቶዶካዊት ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን 

 

የኢትዮጵያ ተክለ ሰውነት ውበት ከላይ በተገለጸበት አንቀጽ ላይ ለረዥም ዘመናት ሲጥቀሱ የኖሩት ዓባይና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ናቸው፡፡ ሁለቱም በኢትዮጵያ ደረት ላይ የበቀሉ የማይነጥፍ ወተት በማምንጨት የማይነጥፈውን ተተካኪ ትውልድ የሚያጠቡ ናቸው፡፡ ኢትዮጵያ በማይነጥፉት በሁለቱ ጡቶቿ በሩቅና በቅርብ ያሉትን ስታጠባ ኖራለች፡፡ ባንዱ ጡቷ (ዓብይ )ከኢትዮጵያ ውጭ ያሉትን ሱዳናውያንና ግብጻውይንን የመሳሰሉትን በጠለልምላሜ እያጠባች፦ በሌላዋ ጡቷ (ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን) በጉያዋ ያሉትን ኢትዮጵይውያንን በቅኔዋ በስነ ጽሑፏ ስታጠባ ኖራለች፡፡ የኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያናችንን ጡትነት ከዐባይ ጡትነት በማስቀደም ከዚህ በታች ለመግለጽ እሞክራለሁ፡፡ 

 

ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን

 

ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን በሚዳቋ ግልገሎች ከተገለጡት ከሁለቱ ኢትዮጵያ ጡቶቿ አንዷ ናት፡፡ “የታተመች  ምንጭ ፏፏቴ ነሽ” ተባለች፡፡ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን፣ ቅኔውን፣ ስነ ጽሑፉን የትወልዱን ስሜት በመመገብ ላይ ያለው ለአራቱ የሙዚቃ ቅኝቶች:- አንቺ ሆየ፣ ባቲ፣ ትዝታና አምባሰል የፈልቀባቸውን ያሬዳዊ ዜማ ያመነጨች ናት፡፡ ቤተ ክርስቲያን በግዕዙ ቋንቋችንና ፊደላችን ትውልድ የሚቀባበለውን ታሪካችንን፣ እምነታችንን ባህላችንን የምታፈስ በኢትዮጵያ ደረት ከበቀሉት አንዷ ጡት ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችን ናት፡፡

በሙዚቃ ትምህርት ርቀው የዘለቁት ሊቃውንት እንደሚሉት የኢትዮጵያ የዘፈን አይነቶች ባንቺ ሆዬ፡ በትዝታ፡ በአምባሰልና በባቲ በአራቱ ቅኝቶች የተመሠረቱት በቤተ ክርስቲያን ዜማወች ቁሜ፣ አጫብር ፣ቤተ ልሔም በሚባሉት ላይ ነው፡፡ የቤተ መቅደሱ ሰለልኩላ ደብር ዐባይ የሚባለው የቅዳሴ ዜማ ሌላው ማእዘን ነው፡፡ ከላይ የተገልጸው አቋቋም የሚባለው አራቱን ማለትም፦ ተክሌ፡ ጎንደር፡ ሳንኳና ፋኖ የሚባሉትም ለዓለማውያን ሙዚቃወቻችን (አጣፋጮች) ቅላጼወች ናቸው ይሏቸዋል፡፡ የራሳቸውን እምነት ይዘው ከውጭ የመጡት የሃይማኖት ሰባኪወች ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ የራሳቸው ዜማ ጥለው ነው፡፡ ስብከታቸውን ከራሳቸው አገር ዜማ ሳይነጥሉ ቢመጡ ኖሮ የሚከተላቸው ኢትዮጵያዊ አይኖርም ነበር ይላሉ፡፡

መናፍቃን (ከፋፋዮች) የኢትዮጵያን ዳር ድንበር ጥሰው በገቡባቸው ወቅቶች ሁሉ እነ መላከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬ “እኔ ተኝቻለሁ ልቤ ግን ነቅቷል” (ማሕ 5፡2) እያሉ የመከላከያ መልዕክት ያስተላልፉ ነበር፡፡ ይህ የኛ ዘመን ነቢዩ ኤርምያስ የነበረበትን ዘመን ይመስላል፡፡ የሀገሩ ጠላቶች የትውልድ አገሩን ለማፍረስ አጋጣሚ እድል ሲጠብቁ ኖረው እድሉ በገጠማቸው ጊዜ “ጠላቶሽ ሁሉ በአንድ ላይ አፋቸውን በኃይል ከፈቱ፡፡ ጥርሳቸውንም አያፋጩ ውጠናታል! የናፈቅነው ጊዜ ይህ ነበር፡፡ ኖረንም ልናየው ነው”(ሰቆቃ ኤር 2፡16) አሉ ብሎ ኤርምያስ የተናገረው በኢትዮጵያ ላይ የደረሰ ይምስላል፡፡

የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ለመበታተን ሲጠብቁ የኖሩ ጠላቶች ግማሾች ቆቡን እየለበሱ ወደ ውስጥ በመግባት፡ ግማሾቹ ቆቡን ሳያወልቁ ከውጭ ሆነው በተሐድሶ ጎራ ተሰልፈዋል፡፡ “በአንድ ላይ አፋቸውን በኃይል ከፈቱ” እንዳለው ነገረ መለኮቱንና ነገረ ማርያም ያልተረዱ ከባእድ ከወረሱት ስህተት ጋራ ቀላቅለው በድፍረት ለመናገር ታጥቀው የተሰለፉበት  እንደዚህ ዘመን የከፋ ዘመን ቤተ ክርስቲያናችንን ገጥሟት የምታውቅ አይመስልም፡፡ 

ነቢዩ ኤርምያስ “ጠላቶችም ሆኑ ወራሪወች የኢየሩሳሌምን በሮች ጥሰው ይገባሉ” እንዳለው፦ ከፓትርያርኩ ጀምሮ የቤተ ክርስቲያናችንን ቀኖና ነገረ መለኮት ሳይጥስ የገባ ማን አለ? “ከነብያት ኃጢአት፣ ከካህናቷም መተላለፍ የተነሳ ሆኖአል” እንዳለውም ከፓትርያርኩ እስከ ተላላኪው ድረስ በሕዝበ ክርስቲያኑ ላይ በደልና ክህደት ያልፈጸመ ማን አለ? “በውስጧ የጻድቃንን ደም አፍሠዋል”(ሰቆ 4፡13)፡ እንዳለውም አሁን ያሉት ጳጳሳት በአርሲ፣ በባሌ፣ በወለጋ፣ በሐረር፣ በሸዋ፣ በጎጃምና በወሎ ለፈሰሰው ደም በዝማታቸው የተሳተፉበት እንደዚህ ዘመን  የከፋ ዘመን ቤተ ክርስቲያናችንን ገጥሟት ያውቃል? ከዚህ ቀጥየ ፏፏቴ ወደ ተባለችው ሁለተኛዋ ጡቷ ወደ ዓባይ እሻገራለሁ፡፡

ዓባይ

 

ከላይ እንደጠቀስኩት በነገረ መለኮትና በሰባዊ ተፈጥሮ ተማሪወች መካከል የተነሳውን ክርክር እንዲዘጋ የተጋበዘ ሰው “ከሳይንሱ ማሕጸን ገብቼ ስዋኝ የሴቱን ማሕጽን ረሳሁት እንጅ በወንድና በሴት መካከል ያለውን ፍቅር ከኔ የበለጠ የሚገልጸው አልነበረም” እንዳለው፦ ስለ ዓባይ ሲነሳ በሊቃውንቱና በባለአገሩ ይነገር የነበረው ሁሉ ትዝ አለኝ፡፡

የሕዳሴው ግድብ የወገንን እልቂት ለማይመለከቱ ወገኖች ደስታቸውን እጥፍ ድርብ አድርጎላቸዋል፡፡ አታሞዋን ይዛ በዐባይ ግድብ መደሰት የነበራባት ጎጃሜዋ እናት ነበረች፡፡ ዳሩ ምን ያድርጋል ግድቡ ሲፈጸም፣ የልጅ አባቷ ሞቶ፣ ልጇ በመከላከል ላይ ሆኖ ቤቷ ፈርሶ በልቅሶ ላይ መሆኗ “የዐባይን እናት ውሀ ጠማት” ሲባል የኖረው ትንግርት የተፈጸመበት ይመስላል፡፡ 

 

የዓባይ ተፋሰስነት እንደ አራቱ ወቅቶች ተለዋዋጭ ነው፡፡ በበጋ፣ በክረምት፣ በመጸውና በጸደይ የፍሰቱን ጠባይ ይቀያይራል፡፡ ከላይ የዝናም ከታች የጎርፍ ማእበል በሚበረታበው በክረምት ይቆጣል፤ ይደፈርሳል፡፡ የዓባይን ውሀ የሚጠጡ ጎልማሶች ወቅቱን ተከትሎ እንደሚቀያየረው እንደ ዐባይ በኢትዮጵያ ላይ ክፉ ዘመን ሲከሰት፣ የውጭ ወራሪወች የውስጥ ባንዳወች መከራ ሲያከብዱባቸው ሕይወታቸው ይደፈርሳል፤ ኑሮ እንደ እንቆቆ ይመራል፡፡ 

“አባይ ሲደፈርስ ሲመስል እንቆቆ

ጋሬጣው ጎጃሜ ገባ ባጭር ታጥቆ” የተባለው የዘመናችንን አደፍራሽ ለመግለጽ ነው፡፡ መንደሩ ፈርሶ፣ ህዝቡ ታምሶ ሳለ ባጭር ታጥቆ ለመከላከል ከተሰለፈው ከጋሬጣው ፋኖ ጎን ከመሰለፍ ይልቅ በመወላወል ላይ ያለውን ፈሪ፦ “ማደሪያ የሌለው ዐባይ ግንድ ይዞ ይዞራል” እየተባለ ተገስጾበታል፡፡

ወራሪ ጠላት ድንብር ጥሶ ዓባይን ተሻግሮ ሲመጣ “አባይም ቢሞላ፡ መሻገሪያው ሌላ” እያለ ከውጭ የሚመጣ ጠላት ባልጠበቀበት ኬላ በመጋረጥ ኢትዮጵያን ያሻግራታል፡፡ ጠላት ከየአቅጣጫወች ከበባ ሲጀምር፦ ምንጩን በመጋራት እየጠጡ ያደጉ ጎልማሶች እርስ በርሳቸው ይጠራራሉ፡፡ የጎጃም ፍኖ ለጎንድር፣ ለሸዋና ለወሎ ፋኖወች ጥሪ ያስተላልፋሉ፡፡ የጎንድር የወሎ የሸዋ ፍኖወች ደግሞ ለሚያዋስኗቸው ኢትዮጵያውያን ጥሪውን ያቀበላሉ፡፡ 

“ካባይ ወዲያ ማዶ አንድ ሰው ተጣራ፣

ወዲህ ማዶ ሆኖ አንድ ሰው አቅራራ፣

ወዲህ ማዶ ሆኖ ሌላ ሰው ወይ አለው፣ 

ጎበዝ ተጠንቀቁ ይህ ነገር ለኛ ነው።” የተባለውም የመላ ኢትዮጵያንን የርስ በርስ ጥሪ ለማንጸባረቅ ነው፡፡ በየዘመናቱ ኢትዮጵያን ፈታኝ ቀን ሲገጥማት ፈሪና ጀግና ተለይቶ የሚታወበት ነው፡፡ ፊሪው ፈርቶ ሲርበተበትና ወደ ኋላ ሲያፈገፍግ፡ ደፋሩ እየፎከረ ይገባበታል፡፡ ይህን ለመግለጽ፦

“ፈሪ ሲርብርተበት ተጠቦ ተጨንቆ፣

ያባይ ልጅ ጎጃሜው ሄደበት ሰንጥቆ” ተብሎ ተዘፈነለት፡፡

ፈሪና ደፋር አብረው ተስልፈው ፈሪው ሸሽቶ ይሮጣል ይፈረጥጣል፡፡ እንደ በላይ ዘለቀ ያለው ጀግና በጀግንነቱ በመዝለቅ ድልን ይቀዳጃል፡፡ ይህንን ለመግለጽ፦

“ያኛው ቁልቁል ሲሮጥ ፈር እየለቀቀ፣

ዐባይ ያሳደገው ያ በላይ ዘለቀ።ተብሎ ተዘፈነለት፡፡

የበላይ ቅኔ ጀግንነት ነው፡፡ የበላይን ጀግንነት ያልተለማመደ ባንዳውን  መቋቋም አይችልም፡፡ በባንዳ ይሸነፋል፡፡   ይህን ለማመልከት፦

“መቀኘት ካቃተው የበላይን ቅኔ፣

ባንዳን ለማሸነፍ አያገኝም ወኔ።” የሚለው ተዘፈነ፡፡ የጎጃም ቆነጃጅቶችና ድረገቦች በላይ በመፋለም ሳለ በሸሸቱ ወንዶች ላይ፡

“ፈርተህ አትንሳፈፍ እንደ በሀር ኩበት፣

እንደ ዘለቀ ልጅ ፎክረህ ግባባት።” ብለው ዘፈኑ፡፡

 

ወንድ ልጅ ለአገሩና ለወገኑ መከታም ጋሻም ነው፡፡ በመከታነቱና በወንድነቱ ካልተጠቀመበት

“በወንድነቱ ወንድ ካልተጠመቀበት፣

ላኩት ወደ በረት አበት ይዛቅበት።” ተብሎ ይዘፈንበታል፡፡

 

ጀግኖች በመዋደቅ ላይ ሳሉ መሰለፉን ትቶ መንደር ለመንደር እየዞረ በሚሰርቀው ዘራፊ ላይም

“የበላይን ቅኔ መቀኘት ካቃተህ፣

ዘራፊ እንዳትሆን ተጠንቀቅ አደራህ።” ተብሎ ተዘፈነበት፡፡

ከላይ የተገለጹት ግጥሞች የሚገልጹት ያባይን ምንጭ እየጠጡ እየዋኙ በመከራ በደስታ ዘምን ያቋረጡትን አሁን በመሞትና በመከላካል ያሉትን ነው፡፡ ከምንጩ ራቅ ብለው የተወለዱ በገባር ወንዞች አማካይነት ለዓባይ ግድብ ባእዳን ባይሆኑም እንደ ጎጃሞች ፉከራውና እስክስታው ፦ 

“አሳ አበላሻለሁ ዓባይ ዳር ነው ቤቴ፣”

ደሮ መረቅማ ክወዴት አባቴ።”  ኢያሉ በመዝፈን ሊያደምቁት አይችሉም፡፡

ዓባይ እንደ አራቱ ወቅቶች ተለዋዋጭ ነው፡፡ በበጋ በክረምት በመጸው በጸደይ የፍሰቱን ጠባይ ይቀያይራል፡፡ በክረምት ከላይ የዝናም ከታች የጎርፍ ማእበል ሲበረታ ይቆጣል፡፡ ይደፈርሳል፡፡ የዓባይን ውሀ የሚጠጡ ጎልማሶች ወቅቱን ተከትሎ እንደሚቀያየረው እንደ ዐባይ ይቀያየራሉ፡፡ በኢትዮጵያ ላይ የመከራው ደመና ሲያንዣብብ የማእበሉ ክብደት ሲያይልባት የጎጃም ጎልማሶች ስሜት ይደፈርሳል፡፡ ሕይወት እንደ እንቆቆ መራራ ይሆንባቸዋል፡፡ ያንዣበባቸውን መሪር  አገዛዝ አሸንቅጥረው ለመጣል ወስነው ይሰለፋሉ፡፡ ይህን ቆራጥ ውሳኔ ለመግልጽ

“አባይ ሲደፈርስ ሲመስል እንቆቆ፣

ጋሬጣው ጎጃሜ ገባ ባጭር ታጥቆ።” ብሎ ባለቅኔው ተቀኘ፡፡

የዐባይ ምንጭ አሳ እንጅ ባህርዩን ቀይሮ ለመታረድ አንገቱን የሚሰጥ ዶሮ አይታቀፍም፡፡ ያባይ ዳር ልጆችም ከመጣው ሁሉ ጋራ በመተባበር ራሳቸውን ቀይረው ለጠላት የሚታረድ ዶሮ አይሆኑም፡፡ ይህን ለመግለጽ

“አሳ አበላሻለሁ ዓባይ ዳር ነው ቤቴ፣”

ደሮ መረቅማ ክወዴት አባቴ።”   የተባለው ተዘፈነ ይባላል፡፡

ጎጃምን በሚያዋስኑት ካዓባይ ወዲህና ወዲያ ማዶ በሚባሉት ሸለቆወች ባሉት ብዙ ገዳማት አድባራትና መስጊዶች ኢትዮጵያውያን ሲቀበሩ ኖረዋል፡፡ ዓባይ ሲያስገብራቸው በኖሩት በ14 ገባር ወንዞች በመላ ኢትዮጵያ ሲቀበሩ የኖሩትን ሁሉ ዐባይ እያጋዘ ለሱዳንና ለግብጽ በማቀበሉ “ዘራፊ” የሚል የቅጽል ስም ነበረው፡፡

“እናት ኢትዮጵያ የገባቸው እዳ፣

ስትወቀስ ኖረች ዘራፊ ልጅ ወልዳ።” እየተባለች  ኢትዮጵያ

በጎጃሞች ስትወቀስና ስትከሰስ ኖራለች፡፡ የሰው ዘር መኖር ከጀመረበት ዘመን ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ  ሲቀበሩ የኖሩትን ኢትዮጵያውያን ሁሉ ግድቡ ተፈጽሞ በቆላ በደጋ የተቀበረው ሰውነታችንን ዓባይ ማጋዙን እስኪያቆም ድረስ በቅኔያችን እይታ በሕይወት ስንኖር እንጅ ስንሞት ኢትዮጵያውያን አልነበርንም።

 

በምንጭነቱና በፈሳሽነቱ የጎጃሞች ባህርይ ሲገለጠበት የኖረው ዓባይ ሲገደብ፡ ምንጩን እየጠጡ ባደጉትና ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ባጠመቀቻቸው ልጆች ላይ አሁን ዛሬ እየተፈመባቸው ያለው ጭፍጨፋና መታረድ ባይኖር ኑሮ፡ አሁን ከቀረበው ዲስኩር ይልቅ የመጠቀ የረቀቀ ቅኔ ይቀርብበት ነበር፡፡ ዳሩ ምን ያደርጋል! በዓባይ ልጆች ላይ ስደቱ መፈናቀሉ መገደሉና መታረዱ በሚፈጸምበት ወቅት ስለ መደመርም ስለ ግድቡም ሲነገርና ሲተረክ የተሰማው ሁሉ “እሬትና ማር” የተቀላቀለበት ባዶ ዲስኩ ሆነ፡፡ በሕዳሴው ግድብ እንደማነኛውም ተወላጅ ደስ ብሎኛል፡፡ በጠ/ ምንስቴሩ የቀርበው የመደመር ፍልስፍና ግን፦ የነበሩትን እሴቶች እንዲሸፈኑና እንዲዘነጉ ከተደረጉባቸው ብዙ አዘናጊወች አንዱ ስለመሰለኝ በግድቡ ደስ ቢለኝም እሬትና ማር ሆነብኝ፡፡ ጠ/ምኒስቴሩ  በዲስኩራቸው ሊነኳቸው ያልደፈሯቸውን ኢትዮጵያ ስትደመርበት የኖረችባቸውን እሴቶች ለመግለጽ ባዘጋጅኋት ጦማር እንገናኝ፡፡

 

ይቆየን 

Monday, 4 August 2025

አቡነ ፋኑኤል የጎረጎሩት ዓሣ ዘንዶ ሆኖ ወጣ!

 አቡነ ፋኑኤል የጎረጎሩት ዓሣ ዘንዶ ሆኖ ወጣ! 

August 2, 2025 

ሐምሌ ፲፱፱ ፳፯፻፯ ዓ.ም. 

መግቢያ 

        አቡነ ፋኑኤል በቨርጂንያ ስቴት አሌክሳንደርያ ከተማ የምትገኘው የሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ በነበረዉ በታደሰ ሲሳይ ላይ በሶስት ካህናት የተላለፈውን ዉግዘት ዉድቅ ለማድረግ ሲሉ አቡነ ፋኑኤል የሰጡት የዉሸት ምክንያት የሚቀጥለው ነው። ይህም የአቡነ ፋኑኤልን ዉሸት ዛሬ የትግራይ ቤተክርስቲያንን ገንጥለው በሚመሩት በአባ ሰረቀ ብርሀን “እውነትና ንጋት” በሚል ርዕስ የተጻፈዉን መጽሐፍ እምቅ የሆነውን ታሪካዊ ሂደት እንደገና ቀስቅሶታል። አቡነ ፋኑኤል ሐሰታቸውን በገለፁበት ደብዳቤው ላይ እንዲህ ብለው ጽፈው ነበር። “...ሦስተኛ አስተርአየ ጽጌ ቀድሞ ቄስ የነበሩ ሲሆን በአሁኑ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ቀደም ሲል የሰሜን አሜሪካ ሊቀ ጳጳስ በነበሩበት ጊዜ አስተርአየ ጽጌ በሃይማኖት ምክንያት ተወግዘው ክህነታቸው የተያዘ ሆኖ እያለ አሁንም በድፍረት የሚቀድሱ መሆናቸው ሀገር ያወቀው ጉዳይ ሆኖ እያለ አውግዣለው ሲሉ ኃፍረት የማይሰማቸው በመሆኑ ድርጊቱ አሳዛኝ ሀኖ አግኝተዋለን…” የደብዳቤውን ሙሉ ይዘት ለማግኘት የሚቀጥለውን ሰንሰለት ይጫኑ “አባ ፋኑኤል የታደሰ ሲሳይን ውግዘት ስለማንሳት የጻፉት ደብዳቤ"። 

        አቡነ ፋኑኤል ስለ ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ ያቀርቡት የሐሰት ሽፋን ከነበረው ሁኔታ ጋር በፍፁም የራቀ ነው። በአጭሩ ጉዳይ እንዲህ ነው። የዉግዘቱ መነሻ በቪርጂኒያ፣ በዲሲና ሜሪላንድ የሚኖረውን ህዝበ ክርስቲያን ያመሰው የታደሰ ሲሳይ ዉድቀት ነበር። በስብሰባው ላይ ተገኝተው ህዝበ ክርስቲያኑ ያቀረበውን የታደሰ ሲሳይን ስህተት ቤተ ክርስቲያናችን በምትመራባቸው መጻህፍት መዝነው ህዝባዊውን ውግዘት ካጸደቁት ቀሳውስት አንዱ ቀሲስ አስተርአየ ናቸው። ቀደም ሲል ከዛሬ 20 ዓመት በፊት መስከረም 22 ቀን 1997 ዓ/ ም (October 2, 2004 CE) በወቅቱ የሰሜን አሜሪካ ሊቀ ጳጳስ በነበሩት በአሁኑ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስና በካንሳስ ኪዳነ ምሕረት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ በነበሩት በቀሲስ አስተርአየ ጽጌ መካከል ውዝግብ ተነስቶ ነበር። ይህንን ተከትሎ አቡነ ማትያስ በቀሲስ አስተርአየ ጽጌ ላይ ጊዚያዊ እገዳ አስተላለፉ። የደብዳቤውን ሙሉ ይዘት ለማግኘት የሚቀጥለውን ሰንሰለት ይጫኑ አቡነ ማትያስ ደብዳቤ በቀሲስ አስተርአየ ላይ የጣሉት ጊዚያዊ እገዳ። 

        ያ ዉዝግብ በሊቀ ሊቃውንት ወርቅነህ ሰብሳቢነት ይመራ በነበረው ማህበረ ካህናት ጉባኤ ተመርምሮ የቀሲስ አስተርአየ ትምህርትና እምነት ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ እምነታና አስተምሮ እንዳልወጣ አረጋግጧል። ሙሉ ዉሳኔውንም በአቡነ ጳውሎስ ይመራ ለነበረው ሲኖዶስ ከመረጃዎች ጋር አያይዞ አዲስ አበባ ልኳል። የማህበረ ካህናቱ ጉባኤም ያንኑ ውሳኔ አያይዞ በስደት ለሚገኘውም ሲኖዶስም ልኳል። አቡነ ይስሐቅ ይህንን ተንተርሰው በቀሲስ አስተርአየ ላይ ተጥሎ የነበረውን የ6 ወር ጊዚያው እገዳውን አነሱት። የደብዳቤውን ሙሉ ይዘት ለማግኘት የሚቀጥለውን ሰንሰለት ይጫኑ አቡነ ይስሀቅ ለክንሳስ ህዝብ በላኩበት ወረቀት እግዳው መነሳቱንተረጋግጧል። 

        አቡነ ማትያስ በዘንዘርጡ ዳንኤል ክብረትና ከፈለኝ በሚባለው ቄስ ምክር እየተመሩ በሊቀ ሊቃውንት ወርቅነህ ሰብሳቢነት ይመራ ከነረው ማህበረ ካህናት ጉባኤ ጋር ተጋጩ። በአቡነ ማትያስና በማህበረ ካህናቱ መካከል ከፍተኛ ዉዝግብ ተነስቶ ማህበረ ካህናቱ አቡነ ማትያስን ገስጿቸዋል። በዚህም ምክንያት በአቡነ ማትያስና በማህበረ ካህናቱ መካከል በተነሳው ከፍተኛ ዉዝገብ ዉስጥ አባ ሰረቀ ብርሀን ዋና ተዋናይ ነበሩ። በዚህ ዉዝግብ ከተሳተፉት ዉስጥ በሞት ከተለዩት ከአቡነ ይስሐቅ፣ አቡነ ገብርኤል፣ አቡነ ጳውሎስና መጋቢ አእላፍ መክብብ በስተቀር ሁሉም በሕይወት ለምስክርነት አሉ። በአቡነ ጳውሎስ ይመራ የነበረው ሲኖዶስ በሊቀ ሊቃውንት ወርቅነህ ሲመራ በነረው የካህናት ጉባኤ ዉሳኔ በመስማማት፣ በዳንኤል ክብረትና በከፈለኝ ምክር የሚራመደውን የአቡነ ማትያስን ሃሳብ ዉድቅ አድርጎታል። አቡነ ጳውሎስ አቡነ ማትያስንና ዳንኤል ክብረትን በቃል ገስጿቸዋል። 

        አቡነ ማትያስ በዘንዘርጡ ዳንኤል ክብረትና በከፈለኝ እየተመከሩ የሚያራምዱትን ሀሳብ ባለማቆማቸው አቡነ ጳውሎስም ሊያስቆማቸው ባለመቻላቸው ጉዳዩ የተነሳበት የካንሳስ ኪዳነ ምሕረት የሚቀጥለውን አደረጉ። ይህ የተነሳው ጉዳይ ቤተክርስቲያናችን ጥንታዊት ኦሮዶክሳዊት መሆኗን ከምታረጋግጥባቸው አስተምሮዎች ዋናውና አንዱ ስለሆነ ለአቻዎቿ ለአሕት ባተክርስቲያንና ለባዛንታን ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት የካንሳስ ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስትያን ምዕመናን ጉዳዩን አቀረቡት። አሐት አብያተ ክርስቲያናትም በሊቀ ሊቃውንት ወርቅነህ ሰብሳቢነት ይመራ በነረው ማህበረ ካህናት ጉባኤ ተመርምሮ የተወሰነውና የቀሲስ አስተርአየ ትምህርትና እምነት ከኦርቶዶክስ እምነታና አስተምሮ እንደሆነ አረጋገጡ። እስከዚህ ቅጽበት ድረስ ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ በአቡነ ማትያስ የተላለፈባቸውን የ6 ወር ጊዚያዊ እገዳ የተሳሳቱ መሆኑን እየገለፁ እገዳውን በማክበር ወደ ቤተመቅደስ ገብተው ኪዳንም አልደርሱም ቅዳሴ አልቀደሱም። ይህንንም በማድረጋቸው ማህብረ ካህናቱ በጣም አድንቆአቸዋል። 

        አባ ፋኑኤል ግብረ አበራቸውን ታደሰ ሲሳይን ለመሸፈንና ቆሞስ ለማድረግ ሲሉ ይህንን ሁሉ በቅርብ ሆነው እያወቁ እንዳልነበረ አድርገው የተነሳውን ጊዜዊ እገዳ ወደ ዉግዝት ቀይሩት። አቡነ ፋኑኤል ግብረ አበራቸውን ለመሸፈን ብቻ ሲሉ የአቡነ ማትያስን ስም ለስህተታቸው መሸፈኛ ማድረጋቸው የመጨረሻ ሀጥያት ነው። 

        ይህ የአቡነ ፋኑኤል ተደጋጋሚ ሐሰት “እውነትና ንጋት” በሚል ርዕስ በአባ ሰረቀ ስም የታተመችው መጽሐፍ የያዘችውን እምቅ ጉዳይ እንደገና እንዲቀሰቀስ አድርጎታል። ከዚህ ቀደም አቡነ ፋኑኤል የሚያደርጉትን ስህተት እንዲያርሙ የተገሰጹበት አባ ፋኑኤል አዲስ ተክል ናቸው የሚለውን ያንብቡ። 

        ከዚህ ቀጥሎ በ“እውነትና ንጋት” የቀረበውን የመጻህፏን ሐተታ አጠር ባለ መልኩ የቀረበ አስተያየት ስለሆነና አቡነ ፋኑኤል የነኩትን በሚከተሉት ገጾች ላይ ቀርቧል።


እውነትና ንጋት 

        ቅዱስ ጳውሎስ “ወኩሎ ዘተጽህፈ ለተግሳጸ ዚአነ ተጽህፈ” ( ሮሜ ) እንዳለው የተጻፈ ሁሉ ትምህርት የተጠሙት እንዲማሩበት፤ ሰነፎችና የሚስቱ እንዲገሰጹበት ተጻፈ። በየዘመኑና ትውልዱ የተነሱ ችሎታ ያላቸውም ይሁን ችሎታ የሌላቸው ጸሀፊወች በነበሩበት ዘመን ለመጉዳትም ብለው ይሁን ለመጥቀም በብዙ መንገድና በተለያዩ ምክንያቶች ይጽፋሉ። በዚህ ነባራዊ ሂደት ኢትዮጵያ ያለፈችባቸውን ዘመንን የትውልዱን ውድቀትና ትንሳኤ ለማሳየት የተመዘገቡትን ሁሉ ሰብስባ ይዛለች። ሰብስባ የያዘቻቸው መዛግብቶች በተገቢው መንገድ እየተጠቀሱ ጎጅውን ተጎጅውን ለማሳየት ቅዱሳት መጻህፍትን እንደ ምሳሌ ተጠቅማለች። 

        ለምሳሌ፦ መጽሀፍ ቅዱስ የእግዚአብሄርን ከሀሊነትና መጋቢነት ለማድነቅ፤ የሰውን ደግነትና ክፋት ለማሳየት፤ የቃየልና ገዳይነትና የአቤልን ተገዳይነት፤ የሙሴንና የአሮንን ብርታትና ድካም፤ የዳዊትን በጎ ባህርይና ክፉ ባህርይ ጎን ለጎን አስቀምጧል። በሀዲስ ኪዳንም የነጴጥሮስና የነጳውሎስንም ድካምና ብርታት የዲያብሎስም ስእል ሳይቀር እናያለን። 

        ይሁን እንጅ ሳጥናዔል ቃዔል ይሁዳ በቅዱስ መጽሀፍ ተመዘገበው ስለተገኙ ማንም በሳጥናኤል ወይም በቃኤል የሚጠራ የለም። ይህ ሁሉ የተዘጋጀው ለውድቀትና ለውርደት ክፉ ምሳሌ የሆነውን እንድንሸሸው፤ የሚጠቅመውን እንድንከተለው እንድንማርበት ነው። አሳሳች ተግባራቸው የሚታፈርባቸውና የምንሸሻቸው እንጅ ተጽፎ ስለተገኙ እንደምሳሌ የምንኮራባቸው አይደሉም። 

        በታላቁ ቅዱስ መጽሀፍ እንደምናየው፤ በጥንታዊነት ዜግነት ጉዟችን ውስጥ የተፈጸሙትን ውድቀትን ትንሳዔ የሚያሳዩ መዛግብቶች በጥንታዊት ቤተ ክርስቲያናችን በመጽሐፍ በቅኔ በገድል በተአምር መልክ ተጽፈዋል። እነዚህ ሁሉ ከኛ በፊት ባለፈው ዘመን የነበሩት ተከታታይ ትውልዶች ያለፉባቸውን የተጎዳዱባቸውን የተደጋገፉባቸውን የወደቁባቸውንና የተነሱባቸውን እንድናይባቸውና የእግዚአብሄርን ዘላለማዊ ታዳጊነት እንድናደንቅባቸው ተጽፈዋል። 

        በኛ ዘመንም ወያኔዎች በዘረጉልን የጥፋት ጎዳና ያለፍንባቸው ውድቀታችንና ትንሳያችን ለማሳየትም ሆነ ለግል ጥቅም በቤተ ክርስቲያናችን ባብነቱ ትምህርት ያላለፉ ልቅ በሆነ መንገድ እያዘጋጁ ለግል ጥቅም ሸጠው ለመጠቀም ሲሉ በደህናው ዘመን ይደረግ እንደነበረው በሊቃውንት ጉባዔ ሳይጠና ሳይመረመር አቋማቸውን እየቀያየሩ የመዝሙርና የተለያዩ ድርሳናት በመድረስ ቤተ ክርስቲያናችንን አጥለቅልቀዋታል።

        ይህችም አባ ሰረቀ ያሳተሟት የዘገባ ስብስብ በዘመናችን የተከሰቱትን ነገሮች ውድቀታችንን ከምናይባቸው መዛግብቶች አንዷ ናት። 

        ከላይ እንዳልነው ቤተ ክርስቲያናችን ከምትደንቅባቸው ብዙ ነገሮች አንዱ ይህንን የመሳሰሉ ያለፈውን ውድቀት የሚያሳዩንን መዛግብት በግምጃ ቤቷ ሰብስባ በመያዟ ነው። ለተለያዩ ጥቅማ ጥቅም ሲሉ አውቀም ሆነ ሳያውቁ በጉባዔ አባቶች ያላስተማሩን ከውጭ እየለቃቀሙ አሳትመው ለገብያ ያቀረቧቸው በግምጃ ቤታችን በመገኘታቸው ፤ለነገረ መለኮትና ነገረ ማርያም ማስረጃ አድርገው በማቅረብ እራሳቸው ተሳስተው ምእመናንንም ከማሳሳታችን በቀር፤ የተጻፈውን ሁሉ ለትምህርት ለትግሳጽ በእቃ ግምጃ ቤታችን መጠበቃቸው መልካም ነው። 

        ይህች እውነትና ንጋት በሚል ስም የታተመችው መጽህፍ አሳታሚው ለምን ብለው እንዳሳተሙት መርምሮ እንዲደርስበት ለተመልካች እየተውን፤ ያለፍንባቸውን ብዙ ፈተናወች ከሚያሳዩን ብዙ መዛግብቶች አንዷ በመሆኗ እንድንገሰጽባት እንድንታዘብባትባና የገባውን ስህተት እንድናርምባት በውስጧ የያዘቻቸውን ዓበይት ቁም ነገሮች ገጽ በገጽ ለመመልከት እንሞክራለን። 

        ይህችን የመዛግብት ክምችት እውነትና ንጋት በሚል ስም አባ ሠረቀ ብርሃን ወ/ ሳሙኤል ታህሳስ 2004 በMega Printing P.L.C አሳተሟት። በአቡነ ጳውሎስ ዘመን በቤተ ክህነቱ አዳራሽ ተመርቃለች። መጽሀፏ በሶስት ክፍል ተደራጅታለች። ሰፊውንና የመጀመሪውን ውዝግብ የያዘችው ከገጽ 18 እስከ ገጽ 80 ያለው ክፍል ነው። ይህ ክፍል ወያኔ በጠቅላላ ቤተ ክርስቲያናችን ከፈጸማቸው ከብዙ አስተዛዛቢ ነገሮች አንዱን ክስተት ብቻ የያዘች የመዛግብት ክምችት ናት። ይህ የመዛግብት ክምችት ዋሸንግተን ዲስ ቅድስ ማርያም ደብር ቀሲስ ዶ/ ር አማረ በአስተዳዳሪነት ሊቀ ሊቃውንት ወርቅነህ የሃይማኖቱ የበላይ ጠባቂነት ይመሩ በነበሩበት ወቅት የተከሰተውን የመከፋፍያ ደባ የሚያሳይ ነው።

        ወቅቱንና በመዛግብቱ የተጠቀሱትን ሰዎች የእውቀት ችሎታ አቋምና የተልእኳቸውን መሰረት ማመልከት ተገደደ። 

ወቅቱ 

        ያ ወቅት በአቶ መለሰና በእሰየ (ወያኔ) መካከል የቤተ ሰብ መከፋፈል ተከስቶ እርስ በርሳቸው ሲናጎዱ የዋሁን የኢትዮጵያን ህዝብ የእርስ በርስ መታግያቸው የሚዳ ሳር ያደረጉበት ወቅት ነበር። አቡነ ጳውሎስ ከመለሰ ጋራ አቡነ ማትያስ ከእሰየ ጎራ ተሰለፉ። በዚህም ምክንያት“ገደሉን ሳያይ ሳር ብቻ እየተመለከተ ገደል እንደሚገባ በሬ አቡነ ማትያስም በወያኔ ደጋፊነታቸው ላይ የሚያስከትልባቸውን ሳይመለከቱ አቡነ ጳውሎስን “ከመከፋፈል ሌላ ማድረግ የመያውቁ ከፋፋይ” ብለው የዘለፉበት ወቅት ነበር። 

        በዚህ ወቅት በኢትዮጵያውያን መካከል በሰፊው ሲነገር እንደነበረው፦ በአቶ ስብሀት ነጋና በገብረ ኪዳን ደስታ ሰልጥነው ጎንደርን ጎጃምን ሸዋን እየሰለሉ ወያኔን ከምንይልክ ቤተ መንግስት ካስገቡት መነኮሳት መካከል አንዱ አባ ሰረቀ ነበሩ። በውስጥ ያልሆነ ነገር እያነሱ ህዝቡን ይከፋፍሉበት ወቅት ነበር። በአገር ውስጥ የነበራቸውን ተልእኮ ከፈጸሙ በኋለ ወደ አሜሪካ ተሻግረው የውጩን ህዝብ ለመሰለል እንደመጡ ይነገራል። ወደ አሜሪካ መጥተው ቅዱስ ጊዮርጊስ በሚል ስም ቤተ ክርስቲያን መስርተው በስደት ላይ ያለውን ህዝብ በመሰለል ላይ ነበሩ። በዚህ ወቅት የመከፋፈሉ መንፈስ በሰፊው ተሰራጭቶ ሁሉንም ከፈለው። 

        አባ ሰረቀ የመለሰ ደጋፊ ሲሆኑ ከአቡነ ማትያስ ጋራ የሚፋለጡበት ዘመን ነበር። በዚህ ወቅት የማይደግፉትን ጎራ ለማስያዝ ይጣደፉ ነበር። በዚህ ወቅት ህዝቡ የሚከፋፈልበት ትንሽ ነገር እየተከሰተ በአገር ቤት የሚደረገው ሁሉ ወደ ውጭም እየወጣ የተሰደደውን ይከፋፍሉ ነበር። በዚህ ወቅት አንዳንድ ሰወች የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ እየመሰሉ ከአዲስ አበባ ወደ ውጭ ይጎርፉ ነበር። 

        ይህች መጽሀፍ ሰብስባ በያዘቻቸው መዛግብቶች የተከሰቱትን የመከፋፍያ ስህተቶች ይዘው ወደከንሳስ የዘለቁት በዲቁና በዘማሪ ስም ከዋናው ካዲስ አበባ የመጡ ነበሩ። “በእንተ ስማ ለማርያም” እያሉ እውቀቱንና ሙያውን እየተማሩ ካደጉት በላይ እናውቃለን የሚሉ ለህዝብ የሚመስል ነገር ፈጠው የማርያም ጠላት ናቸውና አደባድቡን የሚል የመከፋፍያ ሸፍጥ በከንሳስ ኪዳነ ምህረት ቤተ ክርስቲያን ችግር አፈነዳ ። 

        ቀሲስ አስተርአየን መናፍቅ ናቸው የሚል የሀሰት ክስ ማሰራጨት ጀመረ። በጥጉ ያሉትን ሴቶች ዘማሪ ብሎ አደራጀ። እነዚህ ሰዎች በከተማውና በመላ አሜሪካ አሰራጩት። ቀጠሉና ከአቡነ ማትያስ የበለጠ ስለ ቤተ ክርስቲያናችን የሚያውቅ የለምና ይመስክሩልን ብለው ጠሯቸው። አቡነ ማትያስም ከሰንበት ተማሪወች ጋራ በመስማማት፤ የሰንበት ተማሪዎች ትክክል ናቸው ቀሲስ አስተርአየ ክዷል ብለው በማገድ አገልግሎቱን ለለሰንበት ተማሪዎች አስረክበው ወደ መኖሪያ ቤታቸው ተመለሱ። 

        በዘገባው የተጠቀሱት ሰዎች ተልእኳቸው ምን ይመስላል? እነማን ነበሩ? በወያኔ ዘመን ብሄራው አቋማቸው ምንድነው? ። 

        መጽሀፏ አካታ ወደ ያዘቻቸው መዛግብት ዝርዝር ሀተታ ከመግባታችን በፊት በስማቸው ያሳተሟት አባ ሰረቀ ማናቸው? በወያኔ ዘመን ምን አደረጉ? ለምን ወደ አሜሪካ መጡ? ተሰደው ወይስ ተልከው? ወደ አሜሪካ የመጡበት ዘመን ምን ይመስል ነበር? በወያኔወች መካከል ማለት በአቶ እሰየና መለሰ በቤተ ሰብ መካከል ምን ተከሰተ? በአቡነ ማትያስና አቡነ ጳውሎስ መካከል 7 የተከሰተው ድራማ ምን ይመስል ነበር? በአባ ሰረቀና በአባ ማትያስ መካከልስ የነበረው ግንኙነት እንዴት ነበር? የጠቅላላዋ ቤተ ክርስቲያን ይዘት ምን ይመስል ነበር? በእውነትና ንጋት ስም ተሰብስበው በታተሙት መዛግብቶች ውስጥ በተደጋጋሚ የተጠቀሱት ሰዎች እነ ማናቸው? ምን አቋምና ችሎታ ነበራቸው? በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ ያላቸው እውቀትና ችሎታ ምን ያህል ነበር? የተከሰተው ስህተት የማን ነበር? አባ ሰረቀ ለምን ሰብስበው አሳተሙት? ምን አሳሰባቸው? ምን አስገደዳቸው? ለቤተ ክርስቲያን አስበው ነው? ወይስ በግላቸው የመጣባቸውን ችግር ማርገቢያ ለማድረግ? ጥያቄውን እራሳቸውና በወቅቱ የነበሩት የሚመልሱት ነው። 

በመዛግብቱ የተካተቱት 

        የወቅቱን ሁኔታ ከተገነዘብን ወደ ዘገባው ዝርዝር እንሻገራለን። የዘገባውን ዝርዝር ከተረዳን ቤተ ክርስቲያናችን በወያኔዎች የገባችበት አዘቅት እንገነዘባለን። ችግሩ ከገባን ከገባችበት አዘቅት አውጥተን ወደ ነበረችበት አቻወቿ (ኦሬንታል አብያተ ክርስቲያናት) ለመመለስ የሚያቅተን አይኖርም። 

        የመዝገቡ ስብስብ የሰዎችን ድካምና የስርአት የእምነትና የአላማ ጽናት እየገለጠ፤ ቤተ ክርስቲያናችን በምን አይነት ሰዎች አመራር እጅ ላይ እንደወደቀች ያሳያል። ማንም ሰው በቀላሉ ይገነዘብ ዘንድ መጽሀፏ በሰበሰበቻቸው መዛግብት የሚታዩትን በሀሰትን በእውነት መካከል የተካሄደውን ትንቅንቅ ይገልጣል ለጥንካሬና ለጥራት ለሚያዘጋጃት አድማስ ላይ ለመድረስ ለሚደረገው ጥናት ይጠቅማል። ሁለት ተቃራኒ ሀሳብና የእምነት አቋማ ያላቸው ባንድ ጎራ አቡነ ማትያስ በሌላው ጎራ ማህበረ ካህናቱ የተለዋወጧቸውን ሀሳቦች ከዚህ በታች እናቀርባለን። ከአቡነ ማትያስ እንጀምራለን። 

የአቡነ ማትያስና የሰንበት ተማሪወች እምነትና አቋም 

        በብጹእ አቡነ ማትያስና በማህበረ ካህናቱ መካከል የተከሰተው ውዝግብ 33 እስክ 80 ይቀጥላል። አቡነ ማትያስ “እመቤታችንን በተመለከተ የምንከተለው እምነትና ትምህርት እንደሮማ ካቶሊክ ከአዳምና ከሄዋን ውርስ የነጻችው ከመወለዷ በፊት ነው” ይላሉ። ገጽ 39 ይመልከቱ። ቀሲስ አስተርአየ ግን “ቅዳሴ ለመቀደስ ህብስት በጻህል ወይን በጽዋዕ መሰየም አለበት። እመቤታችንም በአዳም በኩል ከነበረው ቁርኝት የተቀደሰችው መጀመሪያ ወደ ህልውና መምጣት ነበረባት” ይላሉ። ገጽ 41 ላይ ይመልከቱ። አቡነ ማትያስ ደግሞ “ቅዳሴ ለመቀደስ ህብስት በጻህል ወይን በጽዋዕ መሰየም አለበት። እመቤታችንም በአዳም በኩል ከነበረው ቁርኝት የተቀደሰችው መጀመሪያ ወደ ህልውና መምጣት ነበረባት በማለታቸው ቀሲስ “ኑፋቄያቸውን በመግለጻቸውና በድፍረት በማስተማራቸው ክህነታቸው ተይዟል” ይላሉ። ገጽ 41 ላይ ይመልከቱ። የቀሲስ አስተርአየ ትምህርትና እምነት ሰምተውት እንደማያውቁ “ይህን ክህደት መቀበል አለብን ነው የቀሲስ አስተርአየ ትምህርት አይገርምም? እያሉ አቡነ ማትያስ ይገረማሉ ገጽ 40 ላይ ይመልከቱ። 

        ከቀሲስ አስተርአየ ደግሞ ምን ይገርመወታል “ይህንን ትምህርትና እምነት ካስተማሩኝ መምህራን የተረከብኩት ሲሆን የመላው ኦርቶዶክስ እምነትና ትምህርት ነው” ይላሉ ገጽ 39 ይመልከቱ። ቀሲስ አስተርአየ ይቀጥሉና፤ “ይህ የነ አቡነ ማትያስ እምነት በ20 አመት ውስጥ የተፈጠረ እምነት እንጅ የተዋህዶ እምነትና አይደለም” ይላሉ። ገጽ 41 ላይ ይመልከቱ። 

        ቀሲስ አስተርአየ በወያኔ ዘመን በሲኖዶሱ ዙሪያ በተሰበሰቡት ጳጳሳት ላይ የሚታየውን ድክመትና ሞራል የለሽነት ታዝበው የተናገሩትን አቡነ “ሲኖዶስ እርስ በርስ የሚደባደብ ነው። አገር የካደ ነው። እንኴን ዶክትሪን ሊያስጠብቅ ሀገርን ማስጠብቅ ያልቻለ ነው” ብለው ባደባባይ ፊት ሲኖዶሱን ተሳድበዋል” ቀሲስ ይህን በመናገር ብቻ አልተወሰኑም፤ “ሊቃውንቱ ሁሉ አፈር በልተዋል። እኔ ብቻ ባሜሪካ እገኛለሁ። ብለው የኢትዮጵያ ኦ ቤ ራሳቸውን ብቻ ሊቅ አድርገው አስቀምጠዋል” እያሉ ቀሲስን ይወቅሳሉ። ይህ ያቡነ ማትያስ ወቀሳ፤ ማህበረ ካህናቱ የቀረበለትን ጉዳይ ከመመልከቱ በፊት የቀሲስ አስተርአየን እድገትና የትምህርት ችሎታ በቤተ ክርስቲያን ያበረከቱትን መመልከት ነበረበትና ቀሲስን ጠየቀ። ቀሲስም ከልጅነታቸው ጀምረው በጉባዔ ትምህርት ብዙ የተማሩ መሆናቸውን በካህናት ማሰልጠኛ ትምህርተ አበ ንስሀና እና አዲሲ የወጣውን ቃለ ዓዋዲ እንዲያስተምሩ የተላኩበትን መረጃ በማቅረብ ያበረከቱትን አስተዋጽኦ፤ የሚያሳይ መረጃ አቀረቡ። ገጽ 32 ላይ ይመልከቱ ። 

        ማህበረ ካህናቱ የቀሲስን ሁኔታ ከተረዳ በኋላ “ቀሲስ አስተርአየ ተራ ሰው አይደሉም የተማሩ ብዙ ያወቁና የሚጽፉ ናቸው። ወደ እልክ የሚያስገባ ነገር ከመጣ ችግሩ ይብሳልና ያስቡበት በማለት አቡነ ማትያስ የሄዱበትን የተሳሳተ መንገድ እንዲያስተካክል ጥያቄ አቀረበላቸው” ገጽ 31 ይመልከቱ። የማህበረ ካህናቱ ጉባዔ “የቀሲስ አስተርአየ ትምህርት ከቅዱሳት መጻህፍት ያልወጣና እምነታቸውም ያልተለየ እንዳልሆነ ተረዳ።” ገጽ 32 ላይ ይመልከቱ። ቀሲስ እምነታቸውና ትምህርታቸው ከጥንታዊት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያናችን ትምህርትና እምነት ላይ በጽኑዕ የተመሰረተ ንደሆነ እያመኑና 0ፕ[የሰንበት ተማሪወችና ያቡነ ማትያስ እምነትና ትምህርት የተሳሳተና በስህተት ያገዷቸው እንደሆነ እየመሰከሩ፤ ለአናርኪነት ምሳሌ ላለመሆን የአቡነ ማትያስን እገዳ አክብረው መቀበላቸው ጉባዔውን አስገርሞታል። ገጽ 41 ላይ ይመልከቱ። 

የማህበረ ካህናቱ እምነትና አቋም 

ከገጽ 56 እስከ 66 ባሉት ገጾች ላይ የሰፈሩት መዛግብቶች እንደሚያመለክቱት ማህበረ ካህናቱ አቡነ ማትያስን እንደተሳሳቱ ተገነዘበ። ማህበረ ካህናቱ አቡነ ማትያስን “የተሳሳቱት እርሰዎ እንጅ ቀሲስ አስተርአየ አይደሉም። ከንሳስ ላይ የፈጸሙትን የተሳሳተ እገዳ ያንሱ” አላቸው። አቡነ ማትያስ ስህተታቸውን ከመቀበል ይልቅ “ቀሲስ ተሳስቻለሁ ከአሁን በኋላም ይህንን የተሳሳተ ትምህርት አላስተምርም ብለው ይቅርታ እንዲጠይቁ ማድረጉ ይቀላል” ብለው የማህበረ ካህናቱን ጥያቄ አልተቀበሉትም ገጽ 42 ይመልከቱ።

        ማህበረ ካህናቱ የቀሲስ አስተርአየን እድገትና የትምህርት ችሎታ በቤተ ክርስቲያን ያበረከቱትን መመልከት ነበረበትና ቀሲስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሊቃውንት ተቀርጸው ያደጉና፤ በካህናት ማሰልጠኛም አዲሲ የወጣውን ቃለ ዓዋዲ እና ትምህርተ አበ ንስሀ እንዲያስተምሩ የተላኩበትን መረጃ በማቅረብ የኦርቶዶክስ ጥንተ ትምህርት እንደነበረ ማህበረ ካህናቱ ተመለከተ” ገጽ 32 ላይ ይመልከቱ። ወደ ዝርዝር በመግባት ውዝግቡን ተመለከተ ። “ካህኑ ተራ ሰው አይደሉም የተማሩ ብዙያወቁ ያወቁና የሚጽፉ ናቸው። ወደ እልክ የሚያስገባ ነገር ከመጣ ችግሩ ይብሳልና ያስቡበት በማለት አቀረበላቸው” ገጽ 31 ላይ ይመልከቱ ። የቀሲስ አስተርአየ ትምህርት ከቅዱሳት መጻህፍት ያልወጣና እምነታ ቸውም ያልተለየ እንዳልሆነ ጉባዔው ተረዳ ገጽ 32 ላይ ይመልከቱ። 

        አቡነ ማትያስ ጉዳዩን በቀሲስ ላይ አክብደው ለማቅረብ “ይህ እምነት በ20 አመት ውስጥ የተፈጠረ እምነት እንጅ የተዋህዶ እምነትና አይደለም። ሲኖዶስ እርስ በርስ የሚደባደብ ነው። አገር የካደ ነው። ስንኴን ዶክትሪን ሊያስጠብቅ ሀገርን ማስጠብቅ ያልቻለ ነው ብለው ባደባባይ ፊት ተሳድበዋል” የሚል በቀሲስ ላይ ሌላ ተጨማሪ ክስ ፈጠሩ ገጽ 41 ላይ መልከቱ። አቡነ ማትያስ “በ20 አመት ውስጥ የተፈጠረ እምነት እንጅ የተዋህዶ እምነትና አይደለም“ ላሉት አቡነ ማትያስ የሰጡትን “በሞት የተለዩት ሊቃውንት በሊቃውንት ተተክተዋል። በህይወት ያሉት ሊቃውንት የቀድሞዎችን ጽኁፎች የሚተኩ ሌሎች መጻህፍት ጽፈው ያበረከቱ መሆናቸውን መረዳት እጅግ አስፈላጊ ይመስለናል” የሚል መልስ ሰጡ ገጽ 42 ይመልከቱ። 

        ከማህበረ ካህናቱ ለቀረበላቸው ጥያቄ በመመለስ ፋንታ አቡነ ማትያስ “ማህበረ ካህናቱ የይግባኝ ሰሚነቱን ስልጣን ከየት አገኘው? በየትኛው ስርአተ ቤተክር ስቲያን መሰረት ነው” የሚል መልስ ሰጡ ገጽ 37 ላይ ይመልከቱ። 

        በማለታቸው ማህበረ ካህናቱም “በዚህ አባባልዎ አንድ ጳጳስ እንደፈለገው ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን የጻፏቸውን መጻህትና ለረዥም ዘመናት ቤተ ክርስቲያን አምናበት የኖረችውን እምነት መሻር መለወጥ ይችላል ማንም ሊቃወመው አይገባም ማለተዎ ነውን? የነገረ ሃይማኖት ውሳኔ ባንድ ጳጳስ ብቻ እንዲወሰን የታዘዘው በየትኛው ህገ ቤተ ክርስቲያን ነው? እነዚህን ጥያቄዎች እንዲመልሱልን ተስፋ እናደርጋለን“ የሚልስ ሰጣቸው። ገጽ 50 ይመልከቱ። 

        የቀሲስ አስተርአየ አቋም ኦርቶዶክሳዊ በመሆኑና የአቡነ ማትያስን እምነትና አቋም ከኦርቶዶክስ ክልል የወጣ በመሆኑ ማህበረ ካህናቱ ከአቡነ ማትያስ ቱ ጋራ ተጋጩ ከገጽ 46 እስከ ገጽ 54 ያሉት ዘገባዎች ይመልከቱ። 

        በመጨረሻም አቡነ ገብርኤል “እንደ እውነቱ ከሆነ ስለ ድንግል ማርያም ያለን እምነት በተመለከተ ከእስክንድርያ ስርአተ ትምህርትና እምነት ባንለይ እጅግ መልካም ነው። ካልሆነ ከኦሬንታል አብያተ ክርስቲያናት መለየትን ያስከትላል።” ከመወለዷ በፊት ቅዱስ ገብርል ወይም ራሱ መንፈ ቅዱስ አነጻት ካልን እናትና አባቷን አንጽቷቸዋል ወደ ማለት ያደርሳል” ብለው በጽሁፍ ገለጹ ገጽ 67 ላይ ይመልከቱ ። 

        “ቤተ ክርስቲያንና አማራውን ሰበርኩት” እያለ ለ27 አመታት የመከፋፍያ ምክንያት እየፈጠረ ሲከፋፍል እንደኖረና የገቡ ስህተቶች እንዲታረሙ የሁሉም ሀላፊነት እንደሆነ ለማሳሰብ ይረዳል። 

        አባ ሰረቀ ማሳተማቸው መልካም ቢሆንም፤ ከማህበረ ቅዱሳን ጋራ በሌላ ነገር በተጋጩበት ወቅት ማሳተማቸው ሌላ ጫጫታ ለመፍጠር እንጅ የገባው ስህተት ባለመታረሙ አሳስቧቸው እንዳልነበረ ታዛቢወች ይናገራሉ። አቡነ ጳውሎስ ሞተው አባ ማትያስ በቦታው መተካታቸውን ቢያውቁ ኖሮ ማሳተም ቀርቶ መዛግብቱን ያጠፏቸው ነበር” ይላሉ። 

(ይኸ መጣጥፍ፣ የብሎገሩ ሀሳብ ሳይሆን፣ የደራሲዎቹ ሀሳብ ነው። በውስጡ ያሉትን ሀሳቦች፣ ለመጠየቅም ሆነ ለመሞገት ከተፈለገ፡Abunepetros1928@gmail.com ደራሲዎቹን መጠየቅ ይቻላል) 

        የወያኔ የጥፋት ዘመን በማለፍና በዮዲት፤ በግራኝ መሀመድና በጣሊያን ወደ ተሰበሰበው የታሪክ ቌት እየገባ ነው። “እውነትና ንጋት” በሚል ርእስ የታተመች ይህች የመዛግብት ስብስብም፤ የወያኔን ዘመነ ሙስና የሚቀጥለው ትውልድ የሚያስብባቸው ብዙ የታሪክ መዘክሮች አንዷ ወደ መሆን ትሻገራለች።

(መጣጥፉ የብሎገሩ ሳይሆን የደራሲዎቹ ነው። ደራሲዎቹን ማግኘት ለሚፈልግ፥ በኢሜል፥

Abunepetros1928@gmail.com

ማግኘት ይቻላል።)

Sunday, 3 August 2025

AN OPEN LETTER TO THE NAACP- written in 1998

WHY DO “ERITREANS” WANT TO BECOME MEMBERS OF THE NATIONAL ASSOCIATION FOR THE ADVANCEMENT OF COLORED PEOPLE (NAACP)? 
AN OPEN LETTER TO THE NAACP! 
 
By Wondimu Mekonnen London, UK 

Beware of the wolf in sheepskin! 




Almost the entire educated population of Africa knows of the sacrifices our brothers and sisters in America have made in their struggle to liberate themselves, first from the direct bondage of slavery, and then, after achieving that tremendous objective, from the ravages of inequality and injustice. Malcolm X, Martin Luther King, … and many others are household names of African youth. You, our brothers and sisters in America, have sacrificed so much to turn America from the graveyard of the blackman into a safe haven for the persecuted. We, in Ethiopia, are proud of you! 

 In the history of your struggle for freedom and equality, Ethiopia occupies a special place. Why is that? We all know the reason. When you were persecuted for being “black” in America, as “ the Negro”, your brothers and sisters in Africa were also taken hostage by the same kinds of people. The mighty European force, which came first with a Bible preaching Christ, a White Christ, and after stealing the people’s hearts and minds, later, with a gun to steal their land and pride, failed when it reached Ethiopia. When they attempted to come in with their perverted Gospel, a living, true Bible awaited them, humbling them with the knowledge that we Ethiopians had first known Christ while Europeans were still dwelling in Caves. They could not bring us, the Ethiopian people, their new God, for the God they sought to preach was alive in Ethiopia and by then had dwelt there for one and a half millennia. The gun could only come through the road torn open by their perverted Gospel. Ethiopia had kept holy the original Bible and its message of loving kindness, and she fought back steadfastly, refusing to accept their tainted Gospel, for the Living Word of God is a two-edged sword in the hands of the faithful. Therefore, they went about wreaking havoc until they had subjugated all of our Black brothers and sisters, all except our small corner of Africa, where we, the original Ethiopians, survived unconquered. 

From that part of Africa, the Horn of Africa, the light of freedom for all Africans continued to flicker, no matter how weak and dim it might have become. All the conquerors, who tried to subdue Ethiopia, one by one, failed and failed utterly to subjugate these last defiant black people. First, the Ottoman Turks attempted to conquer Ethiopia. Ethiopia lost a great deal of land and people to the Turks, but she stood her ground on the very soil that is still her home today, including the land recently rechristened "Eritrea". Then the Portuguese came. They too badly failed. The English were the last but one to nearly occupy her. Yet the invaders soon realised that administering Ethiopia was an impossibility, unleashing a disaster of unprecedented magnitude. They left in peace. All learned their lessons bitterly and in the end left her alone. Finally, one more macho gangster by the proud name of Italy cast its eyes on these freedom-loving people and this beautiful, holy black land. 

The first bitter pill the black man forced Italians to drink took place in 1887 at Dogali, not very far from the present Port of Massawa. At this spot, the invincibility of the adventurist European race was proven as vulnerable as that of any mortal human being, at the hands of an Ethiopian Ras, Alula Aba Nega. An entire contingent of the Italian army, armed to the teeth, was wiped out, leaving only eight people to escape and tell the tale. This event was not considered by the Italians as the victory of courageous Ethiopians, but as the horror of their soldiers being devoured by wild animals. There were cries of outrage, mourning, and gnashing of teeth in Rome, where everyone demanded vengeance. Yet vengeance was not that easy against Ethiopians – The Africans! 

The death of Emperor Yohannes IV gave rise to a period of confusion among Ethiopians. The Europeans were giving arms to each rival group of contenders to the throne and waiting for the right time to strike. It was during this period, in August 1889, that for the first time, Asmara was sacrificed to the occupant white race from Europe. There was no one to guard the city, for everyone was busy holding onto the reins of leadership. It was too late to save Asmara. The Italians quickly settled into dismantling every trace of “Ethiopianness” from the hearts and minds of our people of the Red Sea Coast. Immediately, they changed the name of the newly acquired territory from Behir Medri to "Eritrea." They then launched their psychological warfare against the rest of the Ethiopians. They ruled over the people with a heavy hand and bred among them ignorance and forgetfulness. No Ethiopian in “Eritrea” was allowed to learn beyond the Fourth Grade. Many escaped to the Southern free land and obtained their educations there. The rest were subdued and dehumanized into mindless animals. 

After settling well in Asmara, the Italians used Eritrea as a stepping stone for launching their heavy assault on the remaining territory of Ethiopia to finalize their dream of uniting their ill-gotten Italian territories from Eritrea to Somalia. Menelik, the Warrior King, arose with his people and devastated the power of the “Mighty Whiteman from Europe” once again, in March 1896. This victory opened the eyes and minds of our brothers and sisters under subjugation in Africa. From horizon to horizon, the Victory of Adwa was engraved in the minds of our brothers and sisters. 

From this moment onward, resistance against colonialism mushroomed throughout Africa. Our brothers and sisters in America rejoiced more than anyone else. That was why Ethiopian Orthodox Churches, Abyssinian Baptist Churches, and Ethiopian Methodist Churches everywhere became established and remain well-known to all members of the National Association for the Advancement of Colored Peoples (NAACP.) I come before you now only to invoke your memories. The mischief of the colonialists did not stop there. Although Italy was deterred from penetrating into the deeper heart of the Blackman’s Holy Land, Menelik and his men were unable to push the wretched oppressors into the Red Sea. The reasons reside in the historic fact that the Italians had earlier introduced new human and cattle diseases into Ethiopia, including rinderpest, which had badly hurt our nation. Forcing the Italians to sign capitulation papers and exacting from them a vow never again to try, Menelik left them in "Eritrea." 

However, from that moment on, the Italians began their strategy of avenging Dogali and seeking revenge for their humiliation in Adwa. For the next 40 years, they varied their tactics. They began by working with the local people. They recruited the ignorant and rejected of our subjugated people, those degenerated and humiliated in our lost territories, and refashioned them into Askaris, "local soldiers." This includes kids, which were called "Belilas"


When they grew up, they were called "Askaris". 
They trained these Askaris, both physically and psychologically brainwashing them, to hate their blood brothers in the South. These Askaris thought the blue-eyed Romans that administered them were angels who fed them when happy, and destroyed them when angry. 

The Italians stockpiled weapons of mass destruction, tanks, planes and all modern weaponry to launch their assault against Ethiopia once more in 1935. Our Ethiopian brothers forgot their roots and fought for the colonialist Whiteman against their own people, like mad dogs in service to their Italian masters. The Italians rained down nerve gas by planes from the sky and assaulted us with rocket propellers and grenades from the land. Temporarily, the Italians gained the upper hand with war tactics cowardly planned and inhumanly executed. The last, defiant black nation stood at risk of falling. This moment marked a significant solidarity of “coloured people” across the globe in support of the heroic Ethiopians. Especially our African American brothers and sisters in the US and the Caribbean islands identified themselves with Ethiopians. This was a time many African Americans volunteered to fight for Ethiopia and to die an honourable death alongside their brothers and sisters.
They did so gloriously! They contributed money and fought the Ethiopian war in their own way. Ironically, the majority of the Italian forces who were massacring our people were the newly created Eritrean Askaris. That was the worst pain Ethiopia had to endure. What can you do when your brother becomes your enemy's servant and shoots to kill you? With the help of God and the invincible spirit of Ethiopia, together with the British army and African American support, within five years that ordeal was over. This time, despite their nerve gas and barbaric cruelty, crimes not yet accounted for, despite their sycophant Askaris, the Italians were driven out for good, not only from Ethiopia, but also from the territory they had occupied for 70 years, from “Eritrea.” 

After bitter diplomatic battles with the British, the land and the people were reunited with joy, hoping to become one happy family once more in 1952. 

Alas, the Whiteman left the territory only after burying a time bomb. After the last and decisive victory over the occupying Italians, a question remained: What was to be done with the Askaris. Emperor Haile Sellassie I and his men, ardent Christians, chose the path of reconciliation and forgiveness, in understanding of the conditions under which these people were used by the forces of the occupying enemy. Therefore, no punishment was brought upon a single Askari for the crimes committed against their blood brothers and sisters, forgiving crimes against humanity that involved even mass genocide. The “Eritreans” became once more Ethiopians, without even converting their place names back to their original African forms. They lived everywhere within Ethiopia. They prospered. 

To keep the lost and regained territory, at least economically, at the same level as the Italians left it - although the economic benefit was always for the Italians and never for the local people under occupation - the Emperor pumped every meagre resource into Eritrea. The best schools were opened and Eritreans got the best educations, while the rest of Ethiopia was still illiterate. The best hospitals were built in Eritrea, while millions died of malaria and other curable disease elsewhere in Ethiopia. 

All these benefits failed to win the appreciation and loyalty of the Askaris. They developed a perverted nostalgia for serving their white masters. They continued to rebel against Ethiopia for no reason. They secretly entered into alliances with the enemies of Ethiopia. They stealthily worked at it day and night, forging again the old, Italian grand plans of destruction for Ethiopia. To this very day, they are working towards that goal, and will not rest until they have achieved that final, wicked goal. 

One of the main aims of the children and grand children of the Askaris is the defamation of the struggle Ethiopia waged against colonialism. They desecrated our Ethiopian history and heritage wherever they went. But, what is to be expected from such "Uncle Tom" servants? They are hypnotized and controlled. We often cannot but feel sorry for them. They found sympathisers within Ethiopia and managed to overthrow the military regime following Emperor Haile Sellassie I. They found a regime that would accept carrying out Mussolini’s plans for Ethiopia. They executed these plans to every detail through their chosen puppet regime in Ethiopia. As for themselves, they declared independence and started building their “Piccola Roma.” 

Then on 06 May 1998, however, they have fallen out with their puppet regime in Ethiopia, who refused to accept their orders any longer. With a very lame excuse for conflict, a mythical “Colonial Border”, they opened war over our remaining people, killing tens of thousands and displacing hundreds of thousands of Ethiopians. They are still at it when this open letter is written. To begin with, their question of “respect for colonial borders” is a disgrace to the black race. Ethiopia had never signed into existence any such colonial border with the European invaders. Why should she now be bogged down with their Askari arguments today? 

Recently, I was horrified to learn that the same children of the Askaris who had migrated to America have decided to join one of the sacred communities of the African Diaspora, The National Association for the Advancement of Colored Peoples (NAACP). One wonders, why they might have wanted to do that? The very people who had rejected their own African heritage, the very people who had fought so vigorously to become members of the Arab League, are now pretending to be honourable Blackmen in order to qualify for membership in the NAACP! It might have been acceptable to affiliate with this distinguished and sacred society on an individual basis, but why as a group? Given their idolatrous worship of a Whiteman, what is the purpose of their interest in becoming members of an organisation sworn to fight the injustice of domination by one race over another? 

For many Ethiopians and other Africans, who know the so-called “Eritreans,” it is an open secret. They seek to become part of you just as they became part of Ethiopia, and to work from within you, to eat you like a cancer from the inside out, and destroy your historic solidarity with Ethiopia. I personally protest as a free and proud African against their admission into your sacred society, for I know the underling motivation of this group purportedly seeking your friendship. They are in fact your deadly enemies. 

 I urge you to exercise caution. I implore you to safeguard this wonderful society of and for our African American brothers and sisters. Launch your own research. Find out the validity of my claims for yourselves before admitting this group, who target you for evil motives. Discover and reveal the true motivation behind this sinister move by these so-called “Eritreans”. When you face the truth, you too will be horrified just as I am in this moment forced to write this open letter to warn you. Demand answers to the question: If becoming members of the NAACP is so important to them, why only now, when their leadership is engaged in a life and death struggle to destroy the remaining part of Ethiopia? If their intentions are genuine and pure, you have nothing to lose in patiently awaiting an end to this war. And, in truth, you will yet see who they really are.

Beware of the wolf in the sheep-skin! 
ETHIOPIA REACHES HER HANDS UNTO GOD! 

PS: Dear Web readers, Please forward this open letter of mine to whom it may concern in the NAACP. Thank you very much for your co-operation 

CC: NAACCP National Headquarters 
       4805 Mt. Hope Drive 
       Baltimore, MD 21215Mbr 
       Tel. (410) 358-8900 NAACP 

       Branch Office in Los Angles area
      3910 Martin Luther King Jr. Blvd. 
      Suite 202 Los Angeles, 
      Calif. 90008 
      Phone: (323) 296-2630