Friday 26 April 2013

ፊየል ከመድረሷ ቅጠል መበጠሷ


ፊየል ከመድረሷ ቅጠል መበጠሷ

ወንድሙ መኰንን፣ ሎንደን፣ እንግላንድ 25 April 2013

“ኢሳታዊ ሐረት???” ምን? ጉድ ፈላ። ግዕዙን አረብኛ ተካው ልበል?! ቅዱስ ሚካኤል ወይም ቅዱስ ገብርኤል ሳይሆን፣ ወያኔ ሰሞኑን ክንፉን የዘረጋላቸው የሎንደን ደብረጽዮን ቅድስት ማርያም ጥቂት “ካህናት” በየውሸት መነኲሴው አመራር፣ ጭራሹኑ ሐፍረታቸውን ጥለው፣ ቤተክርስቲያኒቱን በዚህ ዓቢይ ጾም ጥርቅም አድርገው መዝጋታቸው ሳያንስ ወያኔ ብብት ውስጥ ለመሸሸግ ተጥግተው ገና የእግራቸው ጢዛ ንእንኳን ጠፈፍ ሳይል፣ ቋንቋውን አቀላጥፈው መናገር ጀመሩ። “ሐረካት! ሐረካት!” ብለውን አረታ! ይሻላቸዋል። “እየመጣሽ ተኚ” አሉ አባ!



ነገሩ እንዲህ ነው። ሐሙስ ዕለት ከጠዋቱ 5 ሰዓት ከ44 ደቂቃ ላይ “ግርማ” ከሚባል ስም “ESAT HAREKAT.pdf” የተላከ ኢ-ሜይል ደረሰኝ። በቅጡ ሳላነበው፣ አየት አደረግኩትና በሥራ ተወጥሬ ስለነበር፣ የአሜሪካው ጓደኛዬ ግርማ በቀለ ይሆናል፣ “በኋላ አነበዋለሁ” ብዬ ችላ አልኩት። እንደገና ያው ኢሜል በዚያው ስም 6 ሰዓት ከ8 ደቂቃ እንደገና ከቸች አለ። “ሆሆይ! ግርማ ለቀቅ አርግኝ! እኔ ለራሴ መጨረስ የነበረብኝን  ሥራ መጨረስ አቅቶኝ እየተሯሯጥኩ ነው! አትነዝንዘኝ!” ብዬ ሥራዬ ላይ ድፍት አልኩኝ። እንደገና ከ8 ደቂቃ በኋላ ለሶስተኛ ጊዜ ከዚያ ግርማ ያው ኢሜል አቃጨለብኝ። “እዲያ! ችኮ! አልለቀቅከኝም ማለት ነው”  ብዬ ንጭንጭ እያልኩኝና፣ ከፈትኩት! የ-የካው ሚካኤል! “ዓይኔ ነው - ባሌ ነው” አለች አሉ ሴትዮዋ፤ እሱም ሲሰርቅ እሷም ስትሰርቅ በመስመር ተጋጭተው! ሰዎቹ ብሶባቸዋል ማለት ነው! ፈጠጠብኝን ጉድ እዩ!

ይኸ በሕብረቀለማት ያሸበረቀ ጽሑፍ፣ (ሙሉውን ለሚፈልግ በግሉ እልክለታለሁ) እዬዬውን የሚያቀልጠው፣ “ኢሳት ጋዜጣዊ ሐረካት አፋፋመብን” እያለ ነው።  ወይ መከራና ጣጣ! በቃ ወያኔ ከብብቱ እየመዘዘ አዲስ ቃል እየፈበረከ በአቀረሸብን ቁጥር፣ ጀሌዎቹ እየተቀባባሉ ደጋግመው ጆሮአችንን ጭው ማድረጋቸው  ሳያንስ፣ እኛም እንገራረፍበት ገባን ልበል! አንዴ መለስ ዜናዊ ያስቸገረውን ወጣቱን ትውልድ ሊሰድብ ፍልጎ፣ “ወጣቱ ሥራ ፈት ፍንዳታ ነው አለ።” አባባሉ ስሜት እኮ አይሰጥም! በቃ ካድሬዎቹ ተቀባበሉና፣ “ፍንዳታ! ፍንዳታ!” ማለት አመጡብን። ወጣቶቹም ነገሩ ግራ ቢገባቸው “ይኽች ነገር ጥሩ ሳትሆን አትቀርም ብለው ነው መሰለኝ፣ እርስ በርሱ “ወጣት ናት፣ ቆንጆ ናት፣ ወጣት ነው፤ ቆንጆ ነው” ማለት ሲፈልጉ “ፍንዳታ ናት፤ ፍንዳታ ነው” ማለትን አመጡብን! እሺ እሱስ ይሁን አማርኛ ነው፣ ግን ይኽቺ የወያኔ “ሐረካት” ምንድናት! ወያኔ ብዙ ብዙ ቃላት አስተምሮናል። ለምሳሌ፣ “እንተርሀምዌ” የሚባል ቃል ለመጀመሪያ ጊዜ ስሰማ፣ ተርበትብቼ “የድክሺነሪ ያለህ!” (መዘገበ ቃላት) ፍለጋ ገባኹ። እሱም አልረዳኝም። ወንድም ታማኝ በየነ፣ “በጀኖሳይድ” ተከሶ በነበረበት ወቅት ሎንደን ብቅ ብሎ ነበር። ቃሉን ባለማወቁ የተሰማውን ስሜት ነግሮን በሳቅ አፈነዳን። “ምንድነው ‘ጄኖሳይድ’ ብዬ ጓደኛየን ጠየቅኩት” አለ ታማኝ። “‘የሰው ዘር ማጥፋት’ ነው ብሎ ነገረኝ!” ታማኝ፣ እራሱን እንደማከክ እያረገ ቀጠለ። “እንዴ፣ በገንዘብ ማጥፋት ብከሰስ እንኳን ይሁን፣  የሰው ዘር ማጥፋት ግን እምኑ ጋ ቁሜ! ታዲያ አንዳንዴ እራስ ምታቴ ሲነሳብኝ፤ እየተሳሳትኩ ‘ጄኖሳይዴ ተነሳብኝ’ ማለት አመጣሁ” አለ። “ሐረካት!” አሉን የኛ ዘመናዮች! ዕውራን እህቶች ወንድሞቼ! ይቅርታ፣ ይቅርታ! ዕውነት መነገር አለበት። ግን ዕውርን ዕውር ሲመራው መጨረሻው ተያያዞ ገደል ነው። በቀቀኖች!

ስለበቀቀን (parrot) ካነሳን፣ አንድ ነገር ትዝ አለኝ። አንዲት ከበቀቀኗ ጋር ብቻዋን ሎንደን የምትኖር ወይዘሮ ነበረች። ሰው በአንኳኳ ቁጥር ከመክፈቷ በፊት “ማነው” ስትል የሰማ ፓሮት፣ በሩ በተንኳኳ ቁጥር “ማነው” ማለትን ተማረ። ታዲያ አንድ ቀን ጠዋት ወይዘሮዋ ተንስታ ለሥራ ወጣች። አንድ ፖስተኛ መጥቶ በሩን አንኳኳ። “ማነው!” አለ በቀቀን ሆዬ ከውስጥ። “ፖስተኛ ነኝ። በሪኮማንዴ የተላከለዎት ደብዳቤ አለዎት። ፈርመው ይቀበሉኝ።” አለ ፖስተኛ ውጭ ብርድ ውስጥ ቁሞ! በር አልተከፈተለትም! አሁንም አንኳኳ! አሁንም “ማነው” የሚል ጥያቄ ከውስጥ ቀረበለት! ፖስተኛው አሁንም ያንኑ መልስ ሰጠ። በሩ አልተከፈተም። ፖስተኛውና በቀቀኑ እንዲቹ ሲባባሉ ዋሉ። በመጨረሻ ፖስተኛው ላንቃው ደርቆ እራሱን ስቶ ተዝለፍልፎ ወደቀ። ወይዘሮዋ ሥራዋን ጨርሳ ወደቤቷ ስትመለስ አንድ ሰው በሯ ላይ ወድቆ አይታ ደነገጠችና “ማነው!” ብላ ጮኸች! በቀቀኑ ከውስጥ “ፖስተኛ ነኝ። በሪኮማንዴ የተላከለዎት ደብዳቤ አለዎት። ፈርመው ይቀበሉኝ።” አለ። የኛዎቹም በቀቀኖችም ያው ናቸው። “ሐረካት” አሉን? ለዛው ሙጥጦች! ሲያናድዱ!

አሁን በሞቴ “ሐረካትን” በግልጽ ኢሳት ላይ መጠቀማቸው አዲሱን ጌታቸው የወያኔን አንጀት ለመብላት ነው? ለመሆኑ፣ ይኸ “ሐረካት” የተባለውን ቃል ወያኔ ከየት መነተፈችው? እንደመሰለኝ ከሆነ እነዚያ “አል ሀባሽ” (al-Ahbash Islamic sect ) የሚሉት ተለጣፊ እስላሞች (ወያኔ መም “አናሳ” የተባለ ሁሉ እያደንደነች ትለጥፍባቸዋለች) አውሰዋት መሆን አለበት። ወያኔ እንዚህን ተለጣፊዎች ተጠቅ፣ አብዛኛውን የአገራችን የእስልምና ሀይማኖት ተከታዩን ሕዝብ ለመደፍጠጥ ሞክረችእስከአሁን አልተሳካለትም! ወዲፊትም አላህ አይቀናትም! ወያኔ ይኸን ጥራዝ ነጠቅ የአረብኛ ቃል ተውሳ፣ ድራማ ስትሠራ ያዩ የሎንደኑ የውሸት መነኲሴና ደንገጡሮቻቸው እነሱም መወያናቸውን ሊያረጋግጡላት፣ “ኢሳት ቴሌቪዢን ጋዜጣዊ ሐረካት አፋፋመብን” ብለው ኢሪታቸውን ማቀለጣቸው፣ በአንድም ብኩል ያሳዝናል በሌላውም ያስቃል። “ሐረካት” አረብኛ ቃል ሁና ሳለች፣እንግዲህ የበግ ለምድ በለበሱ የወሸት መነኲሴ ተቀደሳ፣ ቤተክርስቲያናችን ስተት ብላ ልተገባ ነው መሰለኝ። ወያኔ፣ ድሮውንም እርጉም የተረገመች እምነት ቢስ ስለሆነ “ሐረካት” ብትለን ያምርባታል። የሚያሳዝነው፣ የእስላም አል-ሀበሾች አባዛኛውን አማኝ ማወናበዳቸው ሳያንስ፣  የኛዎቹ የክርስቲያን አል-ሀበሾች ደግመውለነሱ ካልሆነ ሰርዶው አይብቀል ሆንባቸው ክርስቲያናችንን ለማስነጠቅ “ሐርከውብን (ትርጉሙ ምንም ይሁን ምን) ማረፋቸው ነው።

ለቋንቋው ክብር ቢኖረኝም፣ ቤተክርስቲያናችን፣ በግብጽ ፓትሪያርካት ሥር በነበረችበት ጊዜ እንኳን “አረብኛ” ተጠቅማ አታውቅም ነበር። ያው ግዕዟን ይዛ ስትንገዳገድ ኖረች። ዛሬ ግን፣ ዓይና አዎጣዎቹ የወያኔ አዲስ ፍቅረኞች፣ ታማኝነታችውን ለወያኔ ለማረጋገጥ (ወያኔን እምፕሬስ ለማድረግ)፣ “ሐረካት! ” ብለውን አረፉት!

ይገርማል! ዓይጥ ሞቷን ስትሻ፣ የድመት አፍንጫ ታሸታለች ነው የሚባለው? ኢሳት እንዲያውም አባ ትብዬውንና ደንገጦሮቻቸውን እንተርቪው ለማድረግ ያልቧጠጠው ቋጥኝ አልነበረም።

ተከራከሩና ሀሳባችሁን ግለጡ!” “እምቢዮው”!
እንተርቪው ስጡ!” “እምቢዮው!”

ሌቦች ናቸዋ! በኋላም፣ በስንት መከራና ልመና አይደል፣ ስቱዲዮ ሳይሆን ቤተክርስቲያን  ለዚያውም ሞገደኛውን “አባ” ሳይሆን፣ አለብላቢት ደንገጦሮቻቸውን፣ ያ ሁሉ ጊዜ ሰጥተዋቸው፣ ኢንተርቪው የተደረጉት? አሁን “ሐረካት! ሐረካት!” እያሉ እሳት ላይ ማላዘን፣ ምን ይባላል? አዲስ አበባ ቢሆን እሺ! ግዛታቸው ነው! እዚህ ሕግ አለ።እናንተ ጉደኞች! ይኸ ለሞታችሁ መሆን አለበት! ስትሞቱ እናንተን አያርድርገኝ። ከታጋይ ጳውሎስ ጋር ገሀነም በሯን ወለለ አርጋ ከፍታ እሳቷን አንድዳ ትጠብቃችኋለች። መቼም በጾም ምድር አሰናካላችሁን፣ ቤተክርስቲያናችንን ጥርቅም አድርጋችሁ ዘግታችሁብን፣ መንግሥተ ሰማያት መግባት አታስቡም! ታስባላችሁ እንዴ? “ሊቀ-ሊቃውንታችሁ” የመንገሥተ ሰማያትን ሳያሆን የገሀነምን ቁልፍ ይዞ ነው የሚያሽከረክራችሁ።

የኛዎቹ አዲሶቹ ሐረካውያን፣ “ሐረካትን” ደርሰው ለኢሳት ከመላካቸው ጎን ለጎን፣ የቤተክርስቲያናችንን እንጻ ለወያኔ ሹመኞች የማስረከቡን ሩጫ አጧጡፈዋል። አንድ በምዕራብ አውሮጳ የቤተክርስቲያን አለቃ ነኝ ባይ የቤት መለቅለቂያ፣ ለዚሁ ጉዳይ፣ አዲስ አበባ ሂዶ፣ ወሸታሙን መነኲሴ ካቆመሱት ከአዲሱ ፓትሪያርክ ከአባ ማቲያስ ጋር ተነጋግሮ ተመልሷል። “አቡነ ገብርልና አቡነ ቆስቶስ የተባሉ፣ ለሰማዩም ለምድሪቷም የከበዱ፣ ለሰውም ለመላእክክቱም የገዘፉ፣ ሁለት ተዋጊ አቡናት ታዘው ወደ ሎንደን ጉዞ ጀምረዋል። ፉከራቸው፣ እንሱና የሰኩሪቲ ጥበቃ በተገኘበት፣ ለንደን ደብረጽዮን ቅድስት ማርያምን ለመቆጣጠር ነው። ለመሆኑ እነዚህ አቡናት፣ መስቀል ነው ወይስ መትረየስ ደግነው ነው የሚመጡት? ድንበር ላይ ይፈተሹ! እንግዲህ ለሆሳዕና ቤተክርስትያን ሊክፍቱ እዚህ ያለው ሹመኛቸው የዛተው ዛቻ ለኔም ልትንሹ በግሌ ደርሶኛልእንተያያለን። ታጋይ ጳውሎስ የቀመሷትን ዱላ ሳይቀምሱ እነዚህ አባቶች ቤታቸው አርፈው ቢቀመጡ ለነሱም ለኛም የተሻለ አማራጭ ነበር! ከመጡም፣ ሸቀጣ-ሸቀጣቸውን ሸምተው በሰላም ቢመለሱ መላካም ነገር ነው። አንጡራ ሀብታችንን አንጠፍጥፈን የገዛናትን ቤተክርስቲያን በሕይወት ቁመን እያለን መውሰድ የማይታለም ነው። ዕውን እነዚህ አባቶች የሚመጡት፣ የውሸቱን አባ ለማትረፍ ነው ወይስ ለሌላ? ግሩም! ወገናቸው የሆኑትን ጳጳሳት፣ ከታጋይ ጳውሎስ ደብዳቢዎችና አባ እጅጋየሁ መቸ አዳኗቸው? የዋልድባ ገዳም መነኰሳት “ድረሱልን” እያሉ እሪታ ሲያስተጋቡ፣ መች ደረሱላቸው? ለንደን ወይስ ዋልድባ ይቀርባል? ወይስ ሎንደን ብር ስላለች ነው?

በዓለም ዙሪያ የተበተናቸው የኦርቶዶክ ዕመነት ተከታዮች መዕምናን በሙሉ! በሆሳዕና ዕለት ሎንደን ላለነው ወንድሞቻችሁና እህቶቻችሁ ምሕላ አድርጉልን። ሰልፉም ውጊያውም የእግዚአብሔር ነው።

No comments:

Post a Comment