WONDIMU'S BLOG

This blog is about Ethiopian current affairs, literature, poetry, political, social and cultural issues.

Tuesday, 21 July 2020

የፈንቅል አመራር አቶ የማነ ንጉሴ ለምን እንደጠፋ በዝርዝር የተናገረበትን ቪዲዮ ይዘንላችሁ ቀርበናል ያድምጡ

wondimumekonnen.blogspot.com
Posted by Wondimu Mekonnen at Tuesday, July 21, 2020 No comments:
Email ThisBlogThis!Share to XShare to FacebookShare to Pinterest

Sunday, 12 July 2020

† ከክርስቶስ ፍቅር መከራ አይለየንም!!†




ክርስቲያንና ሚስማር              

ሲመቱት ይጠብቃል 
መከራችን ለክብር ነው።

† በአክራሪ ሙስሊሞችና ጽንፈኛ ብሔርተኞች በኦርቶዶክሳውያን ላይ የደረሰው ዝርዝር
   መረጃ።†

መምህር ታሪኩ አበራ
ሎንዶን





ሰኔ 22  ላይ ከምሽቱ 3፡30  ጀምሮ እስከ ሰኔ 23/2012 ዓ.ም ድረስ በሁለት ቀን ብቻ በአክራሪ ብሔርተኞች እና በአክራሪ እስላሞች 
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አማኞችን ዒላማ ያደረገ ጥቃት ሪፖርት
⛪️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️⛪️

1. ጥቃት የተፈጸመባቸው አከባቢዎች
 👉10 ዞኖች (ምሥራቅና ምዕራብ አርሲ፤ ምስራቅና ምዕራብ ሐራርጌ፤  ምሥራቅ ሸዋ፤  ደቡብ ምዕራብ ሸዋ፤ ጅማ፤ ባሌ፤ሐራሪ ክልልና
 መቱ ሲሆን በጣም አነስተኛ የሆነ ሁከት በቡሌ ሆራ ነበር)
 👉2 የከተማ አስተዳደር(አዲስ አበባ እና ድሬደዋ)
 👉45 ወረዳዎች እና ከተሞች (ቦታዎች)

2. የቤተ ክርስቲያን ቀጠሎ
 👉በባሌ ዞን ኮኮሳ ሆጊሶ መድኃኔ ዓለም ሙሉ ለሙሉ ተቃጥሏል

3. የተገደሉ ምዕመናን በተመለከተ 
 👉በጥቃቱ የተገደሉ ሰዎች ብዛት 67 ሲሆን ሁሉም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አማኞች ናቸው፤ ሌሎች የሞቱ ሰዎች ተብለው የተገለጹት 
ከፖሊስ እና ከመከላከያ ሀይል ጋር በተደረገው የአጸፋ ተኩስ ልውውጥ የሞቱ አጥቂዎች እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡
 👉ከሟቾች ውስጡ አንዱ ካህን መሆናቸው የተረጋገጠ ሲሆን ብዙ ካህናት ላይ የአካል ጥቃት ደርሷል፡፡  
 👉የተጠቁና የሟቾች ብሔርን በተመለከተ፦  አብዛኞች ከኦሮሞ እና አማራ ብሔር ሲሆኑ  ጉራጌ፤ ዳዉሮ፤ ወላይታ፤ ትግሬ እና 
የም ከሟቾች ውስጥ ይገኙበታል፡፡
 👉በዕለቱ ከፍተኛ ጥቃት የደረሰባቸውና በሞትና በሕይወት መካከል ያሉ ብዙ ሰዎች የነበሩ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ ያሉበት ሁኔታ 
አልታወቀም፡፡
 👉በኦሮሚያ ክልል ዝዋይ አዳሚ ቱሉ  በሚባል ቦታ በእነዚህ አጥቂዎች አንድ ቤተሰብ በሙሉ 5 ሰዎች (አባት፤ እናትና ልጆች) 
የተገደሉ ሲሆን ብሔራቸው የሽዋ ኦሮሞ ነው፡፡

4. የሟቾች የአገዳደል ሁኔታ እና የአጥቂዎች የጥቃት መሣሪያ 
 👉ጥቃት አድራሾቹ ለግዲያ የተጠቀሙባቸው መሳሪያዎች፡- ጋዝ ፤ሜንጫ ፤ቆንጨራ፥ ዱላ እና ሽጉጥ ነው፡፡ 















 
👉አንገታቸውን ታርደው የተገደሉ ቢያንስ 12 ሰዎች ናቸው
 👉ከውጭ በር በመቆለፍ በቃጠሎ የተገደለ 1 ሰው 











 👉ተደብድቦ በእንጨት ላይ ተሰቅሎ የተገደለ 1 ሲሆን 
 👉ሌሎች በድንጋይና በዱላ በመደብደብ፤ በጥይት እና አስፋልት ላይ በገመድ በመጎተት የተገደሉ ናቸው፡፡

5. የንብረት ውድመትን በተመለከተ
 👉በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የንብረት ጥቃት የደረሰባቸው ሲሆን ለዘመናት ለፍተው፣ ጥረው ግረው ያፈሩትን ሀብትና ሙሉ 
ንብረታቸውን በማጣት በአንድ ጀንበር አጥተው ተመጽዋች ሆነዋል፡፡ 
 👉ሙሉ በሙሉ በእሳት ተቃጥሎ የወደመ፤  ከፊል ጥቃት የደረሰበት እና ከፍተኛ ዘረፋ የተፈጸመ ሲሆን 
 👉በጥቃቱ፡-
  • በየቦታው አሉ የሚባሉ ኦርቶዶክሳውያን በድጋሚ ላያንሰራሩ ሆነው ንብረታቸው የወደመ ሲሆን ከወደሙ የንብረቶች አይነቶች፦  ኢንተርናሽናል ሆቴሎች፤ ሌሎች ሆቴሎች፤ መኖሪያ ቤቶች፤ ትምህርት ቤቶች፤ ካፌዎች ፤ ምግብ ቤቶች፤ ግሮሶሪዎች ፤ማከፋፈያ ሱቆች/የሸቀጣሸቀጥ፤ የእህል ቤቶች፤  የቤትና የስራ መኪኖች (ከአንድ ቤት እስከ 6 መኪና ድረስ)፤ የኮንስትራክሽን  እንዲሁም የትራንስፖርት መኪኖች  ፤ባጃጅ ፤ሞተር ሳይክል፤ ታሪካዊ ቅርሶች እና የመሣሠሉት ይገኙበታል፡፡
  • በገጠር አካባቢ በማሣ ላይ ያሉ ሰብሎችም እንዲወድሙ ተደርጓል፡፡
6. ከመኖሪያ ቤታቸው የተፈናቀሉትን በተመለከት

 👉በአሁኑ ወቅት ከ7000 የማያንሱ ሰዎች የጥቃቱ ሰለባዎች በመሆናቸው በቤተ ክርስቲያንና በአንዳንድ መጠለያዎች ተጠልለው 
የመንግሥትን ድጋፍ እየጠበቁ ይገኛል

7. ተጨማሪ መረጃዎች

1. ከኦርቶዶክሳውያን ውጭ  ንብረታቸው የወደመባቸው ስለመኖራቸው  

 👉99 በመቶ ጥቃት የደረሰበትና የወደመው ንብረት የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ንብረት ሲሆን በአንዳንድ ቦታዎች በመረጃ 
ስህተት ይመስላል 2 ቦታዎች ላይ የፕሮቴስታንት እና የሙስሊም ንብረት ላይ  ጥቃት ደርሷል፡፡
 👉በግድግዳ ከሚለዩ ቤቶች ውስጥ የአርቶዶክሱ ሲጠቃ የሙስሊሙ ምንም ዓይነት ጥቃት አልደረሰም፡፡
 👉በብዙ ሙስሊም ቤቶች መካከል የሚገኝ የኦርቶዶክስ ቤት ሲጠቃ የሙስሊሞች ቤት አልተነካም /ለምሳሌ፦ ቡኖ በደሌ ጮራ 
ወረዳ/
 👉በብዙ ቦታዎች ጥቃት አድራሾች  “አላሀ ወአኩበር” በማለት ይጨፍሩ እንደነበር በአይን እማኞች ተረጋግጧል /በተለይም 
በምዕራብና ምሥራቅ ሐራርጌ አካባቢ/

2. በዘር አሮሞ ሆኖ የተገደለ ሰው ሰለመኖሩ 
 👉በብዙ ኦሮሞዎች ላይ (በተለይም የሸዋ ኦሮሞ ላይ) የሞትም የንብረት ውድመትም ጥቃት ደርሷል፡፡
 👉በአንዳንድ ቦታዎች ቤት ለቤት በመሄድ የክርስቲያኑን የአንገት ማዕተብ እያዩ ጥቃት ያደረሱ ሲሆን እኔ ኦሮሞ ነኝ በማለት 
ምዕመናን ሊያመልጡ ቢሞክሩም ማዕተብ ያሰረ ኦሮሞ አናውቅም  በማለት የጥቃቱ ሰለባ ሆነዋል፡፡ 

3. ሌሎች
 👉ከሟቾች ውስጥ አራስ ሴት እና አቅመ ደካማ አዛውንት /ከ65-72 ዕድሜ ያላቸው/ ይገኙበታል፡፡ 
 👉ረብሻውን የበለጠ ለማቀጣጠል በማሰብ መጽሐፍ ቅዱስ እና ሌሎች ንዋያተ ቅድሳት ተቃጥለዋል
 👉ብጹዕ አቡነ ሔኖክ የጥቃቱ ዒላማ ተደርገው የነበረ ሲሆን በእግዚአብሔር ቸርነት በሰዎች ጥረትና በጸጥታ ኃይሉ ድጋፍ ከሞት 
ተርፈዋል (ሻሸመኔ ላይ)







 👉የኦሮምያ ፖሊስ በአንዳንድ ቦታዎችላይ /ጅማ፤ ሻሸመኔ፤ ዶዶላ/ ንጹሐን ዜጎች ላይ ተኩሷል 
 👉መከላከያ ሠራዊት እና የፌደራል ፖሊስ እስከ ሰኔ 23/2012 ምሽት ድረስ ትዕዛዝ አልደረሰኝም በሚል በጥቃቱ ወቅት ቆመው 
ይመለከቱ ነበር
 👉ሥጋት ተሰምቷቸው በአዲስ አበባ አንዳንድ ቦታዎች ላይ የቤተ ክርስቲያን ደወል በመደወላቸው ከ10 በላይ የሆኑ የኦርቶዶክስ 
ወጣቶች ሁከት ፈጠራችሁ፣ ረብሽ ቀሰቀሳችሁ በሚል በእስር ላይ ይገኛሉ፡፡

8. ማጠቃለያ አስተያየት

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአክራሪ እስልምና እና የአክራሪ ብሔርተኞች የጥቃት ዒላማ ከሆነች 30 ዓመት 
የሞላት ሲሆን በነዚህ አመታት በጅማ፤ በአርሲ፤ በሐራርጌ ፤በባሌ እና  በሌሎችም አንዳንድ አካባቢዎች ታላላቅ አደጋዎች ደርሶባታል፡፡ 
የሰኔ 2012 ዓ.ም ጥቃትም በአዲስ አበባ ከተማ ከተፈጸመው የጅምላ ውድመት በስተቀር በሌሎች አካባቢዎች ሙሉ በሙሉ በሚባል 
ደረጃ የኦርቶዶክስ ምዕመናንን ዒላማ ያደረገ ለመሆኑ የሚከተሉትን ማሳያዎች እንመልከት፡
 👉ንብረታቸው የወደመባቸው እና በስጋት ምክንያት ሸሽተው በቤተ ክርስቲያን ተጠልለው ከሚገኙ ከ7000 በላይ ተጎጂዎች 
ውስጥ አብዛኞች ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች መሆናቸውን 
 👉ጥቃቱ በደረሰባቸው አካባቢዎች በሚኖሩና ከጥቃቱ ከተረፉ ክርስቲያኖች ባገኘነው መረጃ መሠረት ከሰኔ 22 እስከ 
ሰኔ 23/2012 ዓ.ም ድረስ በእነዚህ ጥቃት አድራሾች ሕይወታቸውን ያጡ ወገኖች ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ የተለያየ 
ቋንቋ ተናጋሪዎች የሆኑ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች መሆናቸው
👉ከተገደሉ ክርስቲያኖች ውስጥ አብዛኞች ብሔራቸው ኦሮሞ ሲሆኑ አንዳንዶቹ ለገዳዩቹ ከጥቃቱ ለመትረፍ እኛ ኦሮሞ ነን ሲሉ 
“እኛ መስቀል ያሰረ ኦሮሞ አናውቅም” በማለት መገደላቸውን በቦታው የነበሩ እና ከጥቃቱ የተረፉ የዐይን እማኞች ገልጸዋል 
በአጠቃላይ ባለፉት 30 ዓመታት በተለይም ደግሞ በለፉት 3 ዓመታት በከፋ መልኩ እየተተገበረ የሚገኘው ከኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች 
ነጻ የሆነች ኦሮምያን መፍጠር የሚለው የአክራሪ እስላሞችና የአክራሪ ብሔርተኞች ጥምር ዕቅድ መሆኑ በአሁኑ ጥቃት በግልጽ የወጣበት፡፡  

ለዚህ ግልጽ ማሳያ ውስጥ 
 👉አንደኛው የጥቃት ኢላማ ሆኑ ተብሎ ከሚነገርላቸው የአማራ ብሔር አባላት ሆነው እምነታቸው የእስልምና የሆኑትን ጥቃቱ 
ያላካተተ መሆኑ ሲሆን 
 👉ሁለተኛው ኦሮሞዎች ሆነው ኦርቶዶክሶች ከሆኑ ኦሮሞ ሆኖ ባለመስቀል አናውቅም በማለት የጥቃቱ ሰለባዎች መሆናቸውን ማየት 
በቂ ማሳያ ነው፡፡ 

ከዚህም በተጨማሪ ከአክራሪ ብሔርተኞች ጋር የሚሠሩት የኦሮሚያ ቤተ ክህነት አደራጆች ኦርቶዶክሱ ክርስቲያን ላይ የተፈጸመውን 
ጥቃት በማስተባበሩ ረገድ ድርሻ እንደነበራቸው በፖሊስ ምርመራ  አንዳንድ ማሣያዎች እንዳሉ የተጠቆመ ሲሆን በቀጣይ ሲጣራና 
ሙሉ መረጃ ሲደርሰን ይፋ የምናወጣው ይሆናል፡፡

በቀጣይም እነዚህ አክራሪ እስላሞች እና አክራሪ ብሔርተኞች ኦርቶዶክስ ክርስቲያኑን እና ቤተ ክርስቲያንን የጥቃት ዒላማ አድርገው 
እየሠሩ መሆኑን መረጃዎች ይጠቁማሉ። መንግሥት ሕግ ለማስከበር በአሁኑ ወቅት እያደረገ የሚገኘው ጥረት በጣም የሚደነቅ ሲሆን 
የእነዚህን የአክራሪ እስላሞች እና አክራሪ ብሔርተኞች ድብቅ አጀንዳ (ኦርቶዶክስን ከኦሮሚያ ማጽዳት) የሚለውን ተረድቶት ይሆን? 
የሚለው ጉዳይ ግን አጠያያቂ ነው፡፡

ውድ  አንባቢዎቻችን ይህ ሪፖርት የተጠናቀረው እስከ ሐምሌ 1 2012 ድረስ በተሰበሰበ መረጃ መሰረት ሲሆን በቀጣይም እየተከታተልን
ተጨማሪ ሪፖርቶች ወደናንተ የምናደርስ መሆኑን እናሳውቃለን።

በጥቃቱ ሕይወታቸው ያለፈውን እግዚአብሔር አምላክ ነፍሳቸውን በአጸደ ገነት ያኑርልን፤ አንገታቸው ላይ ስላሠሩት መስቀል፣ 
ስለ ኦርቶዶክሳዊት ሃይማኖት የተሰዉትን የሰማዕታትን አክሊል ያቀዳጅልን፤ ለቤተሰቦቻቸው መጽናናትን ያድልልን፤ በመከራ በስደት 
በጭንቀት ያሉትን ፈጣሪ በቸርነቱ ይጎብኝልን።
ሐምሌ 01/2012 ዓ.ም
ReplyForward
Posted by Wondimu Mekonnen at Sunday, July 12, 2020 No comments:
Email ThisBlogThis!Share to XShare to FacebookShare to Pinterest

Monday, 27 April 2020

አንበሳና ጣዎስ




አንበሳና ጣዎስ



ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ፣ 27 April 2020

በአማርኛ ጣዎስ (peafowl) እንደምትባል፣ ወንድማችን አቶ ምስጢረ ኃይለሥላሴ ነበር ከሳቴብርሀን መዝገብ ቃላትን አገላብጦ ያስተማርኝ ። እስካሁን ምንነቷንም ገዶኝ ሳላውቅ፣ ላውቃትም ጉጉት አድሮብኝ ባለመፈልግ ብዙም አልተጨነቅኩበትም ነበር። እንዳልምል፣ ሰር ዴቪድ አተንቦሮን (Sir David Frederick Attenborough) ስለምከታተል የበርማዋንም፣ የደቡብ ምሥራቅ ኤሲያዋንም፣ የኮንጎ ስምጥ ሸለቆዋንም አኗኗርና አረባብ በቢቢሲ ናሽናል ጂኦግራፊ ለጠቅላላ ዕውቅት ተከታትዬለሁ። ከአገሬ ጋር የሚያገናኛት ስለሌለ በአማርኛ ስም ይኖራት አይኑራትም ለማወቅ ጓጉቼ አላውቅም ነበር።  ወንድማችን ከነገረኝ በኋላ፣ የግዕዝ መዝገበ ቃላትን ሳገላብጥ፣ ጣዎስ ጉብ ብላ አገኘኋት። በማስሊያ (computer) መስመር መዝገበ ቃላትም ላይ (online) ስፈልጋት እዚያም ጣዎስ ሁና ተገኘች ። እስካሁን አላውቃትም ነበር። ከአሁኑ ጀምሮ ግን አውቃታለሁ። መማር ዕድሜ አይገድበውም ይባል ይለ? ገዚዎቼ ሰንደቄ ላይ እንዳለችው አሽታሮታቸው፣የብሔራዊ አርማዬ አድርገው ሊግቱኝ ሲያሟሙቅኝ ጠርጥሬአለኋ!

ሰሞኑን ስለዚህች የበርማ አሞራ ማሞካሸት በዝቶብኝ ግራ ገብቶኝ ነበር። በተለይ አውራ ጥዎሷን (peacock) ከእንስቷ ጣዎስ (peahen) ጋር ተምታቶባቸው፣ እንደቆንጆ ሴት ሲያስውቧት፣ ግማሽ አካል እህቴ በዚያን ሰሞን፣ የአንዲት ሕጻንን ከሽንት ቤት መቅመጫ ውሀ እያመላለሰች ሌሎቹን ሕጻናት ስታጠጣ የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ሥዕል አጋርታን፣ “አለማወቅ እንዴትጥሩ ነው?” ያለችውን ኢያሰላሰልኩ አለፍኩት። ወንዱን ፒኮክ ሲቲቱ መስላው አዳሜ ሲያሞግስ ማለቴ ነው። የወንድሜ ግጥም ግን እንከን አይወጣውም ነበር።

እንስቷ ጣዎስ (peahen) በሥዕሉ ላይ እንደሚታየው ወንዱ ይሁንታዋን ለማግኘት መከራውን ሲያይ ሴቶ ጸጥ ብላ የምትለቅምው ናት ።

የቤት ዶሮም እኮ የአውራው ላባ ነው የሚያምረው። የሴቷም እስከዚህም ነው። አውራው (peacock) ያንን የሚያብረቀርቀውን ላባ የሚነሰንሰው፣ የሴቲቱን ልብ በፍቅር ለማማለል ነው። አውራ ጣዎሶች ሴት ጣዎስን ለማግኘት በዳንስና በላባቸው ውብት ተወዳድረው ማሸነፍ እንዳለባቸው፣ ከቢቢሲ ባየሁት ተገንዝቤአለሁ። እዚህ ላይ ማንንም ባለማወቅ ለመንቀፍ ሳይሆን (እኔም አላውቅም ነበርና) "ፒኮክ" ሲሉ ወንዱን ማለት እንደሆነ ግንዛቤ እንዲኖረን ነው።

እንግዲህ ወደ ሰሞኑ የሶሻል ሜዲያ (ፌስ ቡክ፣ ቫይበር፣ ዋትስአፕ) የእጅ ስልኬ ላይ “አንብሳውን በ*ፒኮክ” ለውጡት የሚሉ ድምጾች ሲንጫጩብኝ፣ ነገሩ እንዴት ነው ብዬ ማተኮር ጀመርኩ። የየቱን ስል፣ የአዲሱን ብሔራዊ ፓርክ ነው ተባልኩ። አዲሱ ብሔራዊ ፓርክ የት ነው ስል፣ የድሮው የምኒልክ ቤተመንግስት ነው ተባልኩ። ክልጅነቴ ጀምሮ፣ ሳያቸው ያደኩት ሁለት የአናብስት ቅርጽ ወለል ብልው ታዩኝ። ብዙም ስላገናዘብ አካኪ ዘራፌን ቀጥልኩ። በፊስቡክ የሴቷን peahen እና የአውራውን peacock ልዩነት አስረድቼ ይህቺን የአገራችን ወፍ ያልሆነችውን አርማችን እንዳታደርጓት የሚል አጭር መልዕክት አስተላለፍኩ። የአሁኑ ብልጽግና ፓርቲ፣ የድሮው ኢሕአዴግ ደጋፊዎች ዘመቻችውን አጦፉታ! “አንበሳ ጨካኝ፣ ነው፣ አንብሳ የፊውዳሉ ዓርማ ነው፣ አንበሳ ይኸ ነው፣ አንብሳ ያ ነው፣ ... “ፒኮክ” የፍቅር ተምሳሌት ናት፣ “ፒኮክ” የብዝሀነት ተምሳሌት ናት . .. ወዘት (ኧረ ጉድ ነው!) የሚል ጩኸትን አጦፉት ። የሆነውን እንሱም የተረዱ አይመስልም ግን፣ ብልጽጋና ምንም ይሁን ምን የሚሠራው ትክክል ነው ብለው መከራከር ግዴታቸው አድረገው ውስደውታል። “ምናባታችሁን ተሆናላችሁ፣ ዐቢይ ሲፈልግ  ለጅግራ ሐውልት ይሥራ"  አንዱ ያለውን አንድ እምወደውና የማከብረው ወንድሚ አሰራጭትሎት አሳቀኝ። ጅግራ እኮ ያገሬ የቆቅ ዘር ናት ። ሥጋዋንም በልቼአለሁ። መልኳም እንደ ፒኮኮአቸው አይሁን ኢንጂ ያምራል።  ምን ገዶኝ ያስጮኸኝ ነበር እሷም ብትሆን! የነሱ ኝኝኝኝ ወያኔያዊ ካድሬነት ይሉሃል ይኸ ነው። በጥሞና ማስረዳት ሲገባ ይኸ ሁሉ ጡዘት የበለጠ ያነሳሳን እንደሆነ እንጂ ምንም የሚያረግብ አልሆነበረም።

የሆነ መልዕክት ደሞ፣ የጠቃልይ ሚኒስትሩን ፎቶ ይዞ፣ “ፒኮኳን ከመተችት፣ አንበሳውን ምንነት ማወቅ "የሚል ተበተነልን። ጠቅላይ ምኒስትሩ ሥራ ፈትተው መልስ የሰጡን መሰለኝና አዳመጥኩት ። ላንድ አፍታ የተባለው ያዘግጀውን ስለ አንበሳ ታሪክ አውቃለሁ የሚለውን ነው። የሚገርመው፣ አንበሳ ከመጽሐፍ ቅዱስ፣ ከእስራኤሎች መሀል የይሑዳ አርማ መሆንኑና ነገስታቶቻችንም የዚያ ዘሮች ነን ስለሚሉ፣ እነሱ በግድ እንደጫኑብን ተነተነልን። ኧረ ተው! እሺ ኢትዮጵያስ ከይሁዳ አንበሳ ትውሳ ጫንችብን እንበል፣ ቤልጀምስ? ኢራንስ? ማቃዶኒይስ? ነዘርላንድስ? ኖርዌይስ?፣ ዩናይትድ ኪንድምስ (ኢንግላንድ፣ ስኮትላንድ እና ዌልስ) ... ? እነዚህስ ክይሑዳ አንበሳ ውስደው ነው? ኧረ እየተስተዋለ! እነሱን ተውአቸው፣ ኬኒያስ ምን ሁና ነው፣ ሁለት አንበሶችን ብሔራዊ አርማዋ ያደረገችው? እንሱም መሀል የአሁይድ ዘሮች ኑረው ነው?

መለስተኛ ጥሩ ነው የምለው መልስ የምጣው ከሲሳይ አጌና ነበር።

ሲሳይ እንደሚለን ከሆነ፣ ሌሎቹ እንዳናፈሱት፣ ከምኒልክ ቤተመንግሥትም ሆነ፣ ከኢዩቤሊዩ ቤተመንግሥት ላይ የነበሩት አንበሶች ተነስተው ሳይሆን፣ ደርግ ለአሥረኛው በዓሉ ያሠራው አዳራሽ መግቢያ ላይ ለ“ፒኮኮቹ” ሐውልት እንደተሠራ አስረዳን። በጣም ጥሩ። እኛ አንበሳው ከታሪካችን ጋር የተያያዘ ነው ብለን መከራከር ስንጀምር፣ የአንበሳው ጠላቶች ደሞ “ምን አገባችሁ፣ ዐቢይ ጥሩ ነገር ሠራ። ለፒኮክ ብቻ ሳይሆን ለምን ለጅግራም ሐውልት አይሠራም ብለው ለመከራክር አኮብኩበው ሲነሱ፣ ሁለታችንም ስህተት ላይ ወደቅን። እኛ ለምን አንበሳችን በዚህች ባዕድ አሞራ ይለወጣል ብለን ስንከራከር፣ እነሱም ደሞ የተለወጥላቸው መስሏቸው ጭፈራ ጀምረው ነበር። ሁላታችንም ተሳስተናል። ሕዝቡን ይቅርታ እንለምን።

ሲሳይ በዚሁ ቢያቆም ጥሩ ነበር። አለፍ አለና፣ እሱም ስህተት ሠራ። ፒኮኮ ለአገራችን አዲስ አይደለችም አለ። ምሳሌም ሲያመጣ፣ ፒኮክ ካፌና ፒኮክ መናፈሻ የታወቁ መጠሪያ ስሞች ናቸው ብሎን እርፍ። ወዳጄ ሲሳይ፣ በአዲስ አበባ፣ ፒኮክ ካፌም ገቢቼ ተሰትናግጄአለሁ፣ ቢኮክ መናፈሻም ሄጄ ተዝናንቼአለሁ። አይገርምህም፣ ያኔ ጣዎሷ እየተሽኮረመመች ባጠገቤ ብታልፍ፣ ፒኮክ መሆኗን ባላወቅኳት ነበር። የአዲስ አበባ የአገልግሎት የነግድ ቤቶች፣ ምን የማይጠሩበት የውጭ ስም አለና! ሎባርዲያ ገብቼ ብልቼአለሁ፣ ሎምባርዲያ ምን እንደሆነ እስከዛሬ አላውቅም። ኤንሪኮ ገብቼ አሮስቶ አዝዤ አንክቼአለሁ። እኒሪኮ የሰው ይሆን የ’እንስሳ ስም መሆኑን አላውቅም። የቦታ ስምም ሳይቀር ተለውጦብናል። ለመሆኑ፣ ካዛንቺስ በጣሊያንኛ የሰራተኛ ሰፈር መሆኑን፣ ፒያሳስ መሀል ከተማ (city centre) መሆንኑ ስንቶቻችን ነው የምናውቀው? ቨኑስ፣ እላፎንቴ እና የመሳሰሉት የምሽት ዳንስ ክበቦች እንዳሉ አውቅ ነበር። እነዚያ ስሞች አማርኛ ነበሩ? ፒኮክ እማ የታወቀ ቢሆን ኑሮ በአማርኛ ጣዎስ ካፌ ይሉት ነበር። ለመዘነጥ ሲባል የውጭ ስም ተሰጣችው እንጂ “ባለውለታዋን” ጣዎስ ለማስታውስ አይደለም። ምሳሌው ውሀ አይቋጥርም።

ለማጠቃለል፣ ብልጽና ቢፈልግ፣ ፒኮኳን አርማው ሊያደርጋት ይችላል። ማንም የሚከለክለው የለም። ጓደኛዬ እንዳለው፣ ሞአ ጣዎስ ዘእምነገደ … እያሉ ቢቅጥሉ ምን ገዶኝ! ግን ልክ አሽታሮቷንን በሰንደቅ ዓላማችን ላይ ትላንት እንደለጠፋችሁኋት፣ ዛሬም፣ ፒኮክን የብሔራዊ ዓርማ ለማድረግ እንዳትሞክሩ ከመማጸን ጋር እጠቅያቸዋለሁ። “የዘፈን ዳርዳሩ እስክስታ ነው” ማን ነበር ያለው?

እግዚአብሔር ከተደቀንብን ወረርሺኝ ህላችንንም ያትርፈን።

Posted by Wondimu Mekonnen at Monday, April 27, 2020 1 comment:
Email ThisBlogThis!Share to XShare to FacebookShare to Pinterest

Wednesday, 11 March 2020

በነገራችን ላይ! ዋለልኝ መኮንን የህይወቱ… የመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች| E10 - Benegerachin Lay [Arts ...

Posted by Wondimu Mekonnen at Wednesday, March 11, 2020 1 comment:
Email ThisBlogThis!Share to XShare to FacebookShare to Pinterest
Newer Posts Older Posts Home
Subscribe to: Posts (Atom)

Blog Archive

  • ▼  2026 (1)
    • ▼  June (1)
      • ታምነን ከማጉደል ይሰውረን!
  • ►  2025 (4)
    • ►  October (1)
    • ►  August (2)
    • ►  January (1)
  • ►  2024 (3)
    • ►  November (1)
    • ►  May (1)
    • ►  March (1)
  • ►  2023 (3)
    • ►  July (1)
    • ►  June (1)
    • ►  February (1)
  • ►  2022 (4)
    • ►  September (1)
    • ►  June (1)
    • ►  January (2)
  • ►  2021 (16)
    • ►  December (2)
    • ►  November (2)
    • ►  October (2)
    • ►  July (3)
    • ►  June (1)
    • ►  April (1)
    • ►  February (4)
    • ►  January (1)
  • ►  2020 (13)
    • ►  December (1)
    • ►  November (2)
    • ►  August (1)
    • ►  July (6)
    • ►  April (1)
    • ►  March (1)
    • ►  January (1)
  • ►  2019 (3)
    • ►  December (1)
    • ►  October (1)
    • ►  January (1)
  • ►  2018 (2)
    • ►  June (2)
  • ►  2017 (3)
    • ►  March (1)
    • ►  January (2)
  • ►  2016 (5)
    • ►  November (1)
    • ►  September (3)
    • ►  July (1)
  • ►  2015 (2)
    • ►  February (1)
    • ►  January (1)
  • ►  2014 (15)
    • ►  December (2)
    • ►  November (3)
    • ►  September (1)
    • ►  July (2)
    • ►  June (5)
    • ►  April (1)
    • ►  March (1)
  • ►  2013 (19)
    • ►  December (1)
    • ►  November (3)
    • ►  October (2)
    • ►  September (3)
    • ►  August (1)
    • ►  July (1)
    • ►  June (1)
    • ►  May (3)
    • ►  April (2)
    • ►  March (1)
    • ►  January (1)
  • ►  2012 (13)
    • ►  October (3)
    • ►  May (1)
    • ►  April (1)
    • ►  March (3)
    • ►  February (4)
    • ►  January (1)
  • ►  2011 (23)
    • ►  December (3)
    • ►  November (1)
    • ►  October (1)
    • ►  September (7)
    • ►  August (3)
    • ►  June (2)
    • ►  May (2)
    • ►  April (2)
    • ►  March (1)
    • ►  February (1)
  • ►  2010 (20)
    • ►  December (2)
    • ►  November (5)
    • ►  October (4)
    • ►  September (5)
    • ►  June (1)
    • ►  May (3)

My web links

  • Ethiopian Current Information Centre
  • Addis Voice
  • EMF
  • Ethiomedia

Followers

Simple theme. Theme images by luoman. Powered by Blogger.